
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 4/2017(ኢዜአ)፦በማህበራዊ ሚዲያዎችና በኢንተርኔት የሚፈጸሙ የማጭበርበር እንቅስቃሴዎች እየበረከቱ ይገኛሉ።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ከዚህ ጋር ተያይዞ እያጋጠሙ ያሉና ሊያጋጥሙ ይችላሉ ያላቸውን ስጋቶች መከላከል የሚያስችሉ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስቀምጧል።
የዲጂታል ማጭበርበሮችን ለመከላከል ልንወስዳቸው የሚገቡ የጥንቃቄ ርምጃዎችንም እንደሚከተለው አቅርቧል፦

ያልታወቁ አድራሻዎችን ወይም ሊንኮችን ከመክፈት በመቆጠብ፤ ከላይ ያሉትን ወይም ተመሳሳይ አድራሻዎች በመልዕክት፣ በማህበራዊ መገናኛ፣ ወይም በሌላ መንገድ ከደረስዎ ከመክፈት መቆጠብ በተለይ “እንኳን ደስ ያለህ! ገንዘብ አሸንፈሃል፣ ይህን አገናኝ ጫን” የሚል መልዕክት ከመጣ፣ ይህ ማጭበርበሪያ ሊሆን ስለሚችል መጠንቀቅ፤

የሞባይል እና የባንክ መረጃዎችን ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ በመጠቀም፤ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎችን ከታመኑ ምንጮች (እንደ Google Play) ወይም አፕስቶር (app-store) ብቻ ያውርዱ።

የይለፍ-ቃልዎን ወይም የባንክ መለያዎችን ባልታወቁ ድረ-ገፆች ከማስገባት መቆጠብ፤

በዲጂታል ሚዲያዎች አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከቱ ሪፖርት በማድረግ፤ እንደዚህ አይነት መልዕክቶች ወይም አድራሻዎች ካዩ፣ ወዲያውኑ ለEthio-CERT በኢ-ሜይል ([email protected]) ወይም በስልክ (933) ያሳውቁ፤

በነፃ Wi-Fi ስንጠቀም በጥንቃቄ በመጠቀም፤ በካፌዎች፣ በሆቴሎች፣ ወይም በሌሎች የህዝብ ቦታዎች ያለውን ነፃ Wi-Fi ሲጠቀሙ፣ የግል መረጃዎችን አያስገቡ።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025