
ዲላ፤ሚያዚያ 4/2017 (ኢዜአ) :-የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተኪ ምርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በስራ እድል ፈጠራ የተሻለ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የሲዳማ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) ተናገሩ።
የሲዳማ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የፓርኩን የስራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።
የፓርኩ የቦርድ ሰብሳቢና የሲዳማ ክልል ልማትና ፕላን ቢሮ ሀላፊ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በፓርኩ 8 ፋብሪካዎች በአቮካዶ ዘይት፣ በወተት፣ ማርና ቡና ማቀነባበር ወደ ስራ ገብተዋል።
በዚህም በተኪ ምርትና በቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም በስራ እድል ፈጠራ የተሻለ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በተለይ በግብርና ምርቶች አቅርቦት 136 ሺህ በላይ በህብረት ስራ የታቀፉ አርሶ አደሮች የገበያ ትስስር በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረጉን አንስተዋል።
ጉብኝቱ የፓርኩን ተሞክሮ ከማስፋት ባለፈ በምርት አቅርቦት ትስስር የተጀመረውን ግንኙነት ለማጠናከር ወሳኝ እንደሆነም ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳደርና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፓርኩ በአካባቢው የገበያ ትስስር እየፈጠረ ነው ብለዋል።
ይህም ግብርናውን በማዘመን የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባሻገር የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲነቃቃ እድል መፍጠሩን ማየታቸውን አንስተዋል።
በቀጣይ አርሶ አደሩ ምርታማነትን በማሳደግ በዘርፉ ያሉ እድሎችን እንዲጠቀም ከማገዝ ባለፈ በክልሉ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በመቅረፍ የአግሮ ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ፤ የመስክ ምልከታው በክልሉ መካከለኛ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን በሙሉ አቅም ወደ ስራ ለማስገባት የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ነው ብለዋል።
በቀጣይ የግብዓትና የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነቶችን በመቅረፍና በፓርኮቹ መካከል የተፈጠረውን ትስስር በማጠናከር የፓርኮቹን ውጤታማነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በጉብኝቱ የሁለቱ ክልሎች የቦርድ ሰብሳቢዎችና አባላት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም አጋርና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025