
ዲላ፤ሚያዚያ 4/2017 (ኢዜአ) :-የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተኪ ምርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በስራ እድል ፈጠራ የተሻለ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የሲዳማ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) ተናገሩ።
የሲዳማ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የፓርኩን የስራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።
የፓርኩ የቦርድ ሰብሳቢና የሲዳማ ክልል ልማትና ፕላን ቢሮ ሀላፊ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በፓርኩ 8 ፋብሪካዎች በአቮካዶ ዘይት፣ በወተት፣ ማርና ቡና ማቀነባበር ወደ ስራ ገብተዋል።
በዚህም በተኪ ምርትና በቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም በስራ እድል ፈጠራ የተሻለ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በተለይ በግብርና ምርቶች አቅርቦት 136 ሺህ በላይ በህብረት ስራ የታቀፉ አርሶ አደሮች የገበያ ትስስር በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረጉን አንስተዋል።
ጉብኝቱ የፓርኩን ተሞክሮ ከማስፋት ባለፈ በምርት አቅርቦት ትስስር የተጀመረውን ግንኙነት ለማጠናከር ወሳኝ እንደሆነም ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳደርና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፓርኩ በአካባቢው የገበያ ትስስር እየፈጠረ ነው ብለዋል።
ይህም ግብርናውን በማዘመን የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባሻገር የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲነቃቃ እድል መፍጠሩን ማየታቸውን አንስተዋል።
በቀጣይ አርሶ አደሩ ምርታማነትን በማሳደግ በዘርፉ ያሉ እድሎችን እንዲጠቀም ከማገዝ ባለፈ በክልሉ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በመቅረፍ የአግሮ ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ፤ የመስክ ምልከታው በክልሉ መካከለኛ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን በሙሉ አቅም ወደ ስራ ለማስገባት የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ነው ብለዋል።
በቀጣይ የግብዓትና የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነቶችን በመቅረፍና በፓርኮቹ መካከል የተፈጠረውን ትስስር በማጠናከር የፓርኮቹን ውጤታማነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በጉብኝቱ የሁለቱ ክልሎች የቦርድ ሰብሳቢዎችና አባላት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም አጋርና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026