የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በጉራጌ ዞን በበጋ መስኖ ከለማው መሬት ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል - መምሪያው

Apr 14, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን ዘንድሮ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት እስካሁን ድረስ ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በዞኑ በበጋ መስኖ 25ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መልማቱን ተናግረዋል።

ከዚህም ከ6 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እስካሁን ድረስ ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ መሰብሰቡን ጠቁመዋል።

በዞኑ በመስኖ ልማት በቆሎ እና ድንች ማልማት እምብዛም የተለመደ አይደለም ያሉት አቶ አበራ፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ግን ከፍራፍሬና አትክልት ልማት ቀጥሎ በቆሎና ድንች በመስኖ ማልማት እየተለመደ መምጣቱን ገልጸዋል።


ምርታማነትን ለማሳደግም ሳይታረሱ የኖሩ እና ባህር ዛፍ የነበረባቸውን መሬቶች ዛፉን አንስቶ በማልማት የአርሶ አደሩንና የወጣቱን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

የአትክልትና ፍራፍሬ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ በወቅቱ ግብአት ከማቅረብ ባለፈ በግብርና ባለሙያዎች ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በበጋ መስኖ ልማት ሥራ ከተሰማሩ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ የእኖር ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር ደሊል ሸምሱ እንዳሉት በመስኖ የተለያዩ አትክልቶች፣ ፍራፍሬና ሰብል ልማት እያከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመጀመሪያ ዙር የመስኖ ልማት ሽያጭ ከ300ሺህ ብር በላይ ገቢ ማገኘታቸውን ገልጸው፣ በአሁኑ ወቅት በሁለተኛ ዙር መስኖ ያለሙት አትክልት ለሽያጭ መድረሱን ተናግረዋል።


ሌላው በወረዳው በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት አቶ አሚኑ ነጂሙ በበኩላቸው፣ በመስኖ ካለሙት የአትክልትና የሰብል ምርት ውጤት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል።

በዞኑ ቸሃ ወረዳ የባህር ዛፍ ተክልን በማንሳት በሁለት ሄክታር ማሳ ላይ ዝንጅብል፣ አቮካዶና የተለያዩ ሰብሎችን የሚያለሙት አርሶ አደር አዳነ ሹሜም እንዲሁ ከልማቱ ከ500ሺህ ብር በላይ ትርፍ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025