የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ በኮንፈረንስ ቱሪዝም ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች - ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ

Apr 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 5/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ኢትዮጵያ በኮንፈረንስ ቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቧን የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ አስታወቁ።

የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ ዓመት የ100 ቀን አፈጻጸም እና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ ያለፉት ዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።

ሚኒስትሯ የዘርፍ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ ከዚህ ቀደም ባልነበረ መልኩ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት ሲሰራበት የቆየው የኮንፈረንስ ቱሪዝም መሆኑን ገልጸዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከ60 በላይ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ እንዲሁም ቀጣናዊ ጉባኤዎች መስተናገዳቸውን አስረድተዋል።

ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አኳያ በእጥፍ ብልጫ ያለው መሆኑን ገልጸው፤ ለዚህም መንግስት አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶችን ከማመቻቸት አንጻር በርካታ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።

መዳረሻዎችን በማልማት በኩልም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሰፋፊ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰው፤ ነባር የቱሪዝም ሀብቶችን የማላቅ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በተለያዩ ዓለም አቀፍ ትልልቅ መድረኮች በመሳተፍ የኢትዮጵያን የዘርፉን እምቅ አቅም ማስተዋወቅ መቻሉንም ተናግረዋል።

እንዲሁም አሁን ያለውን የቱሪዝም ዘርፍን እይታ በሚመጥን መልኩ የፖሊሲ ክለሳ መደረጉንና ይህም በመገባደድ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026