
ሐረር፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የኮሪደርና የቱሪስት መስህብ ልማቶች የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር ማድረጉን የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ቅርስ ቢሮ አስታወቀ፡፡
በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የክልሉን የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች ከጎበኙ ከ130ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ከ136 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱም ተገልጿል።

የቢሮው ሃላፊ አቶ ተወለዳ አብዶሽ እንደገለጹት ቢሮው የክልሉ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን በማስተዋወቅና በማልማት የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር አድርጓል።
የቱሪስት መስህቦች ልማት ከተካሄደባችው መካከልም የዓለም አቀፍ ቅርስ በሆነው ጀጎልን ጨምሮ ሌሎች የኮሪደርና የመስህብ ስፍራዎችን የመንከባከብ፣ የመጠበቅና የማስዋብ እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ለጎብኚዎቹ ቁጥር መጨመር ጉልህ ሚና ማበርከታቸውን አመልክተዋል።
እንዲሁም በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ድርጅት(ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የሸዋል ኢድ በዓል አከባበርም ለጎብኚዎች ቁጥር መጨመር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።

በሐረሪ ክልል በቱሪስቶች ከሚጎበኙት ቅርሶች መካከል የዓለም ቅርስ የሆነው የጀጎል ግንብ፣ በውስጡ የሚገኙ ጥንታዊ መኖሪያ ቤቶችና አምስቱ የጀጎል ግንብ መግቢያ በሮች ይገኙበታል።
በተጨማሪም ባህላዊ የዕደ ጥበብ ውጤቶች፣ የፈረንሳዊው ባለቅኔ አርተር ራንቦ መኖሪያ ቤት፣ የሐረሪ ብሔረሰብ ሙዚየሞች፣ አድባራት፣ የጅብ ምገባ ትርኢትና ሌሎችም በቱሪስቶች የሚገበኙ ጥንታዊ፣ ሃይማኖታዊና ታሪካዊ የመስህብ ስፍራዎች ናቸው።
በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት የክልሉን የመስህብ ስፍራዎችን 7ሺህ 877 የውጭ ቱሪስቶች ጎብኝተዋል ያሉት ሃላፊው፤ ይህም ከዓምናው ጋር ሲነጻጸር በ31 ነጥብ 6 በመቶ ብልጫ እንዳለው ነው የገለጹት።
በተጨማሪም ከ123ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች በክልሉ የሚገኙ የመስህብ ስፍራዎችን መጎብኘታቸውን ገልፀው፤ ይህም ከዓምናው በ7 ነጥብ 4 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን አክለዋል።
ከዚህ ጎን ለጎን የተከናወነው የኮሪደር ልማት ግንባታና የማስዋብ ሥራዎቹ ከተማውን ለቱሪስቶች ምቹና ውብ እንዲሆን ማስቻላቸውንም አቶ ተወለዳ ገልጸዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026