
ሐረር፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የኮሪደርና የቱሪስት መስህብ ልማቶች የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር ማድረጉን የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ቅርስ ቢሮ አስታወቀ፡፡
በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የክልሉን የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች ከጎበኙ ከ130ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ከ136 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱም ተገልጿል።

የቢሮው ሃላፊ አቶ ተወለዳ አብዶሽ እንደገለጹት ቢሮው የክልሉ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን በማስተዋወቅና በማልማት የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር አድርጓል።
የቱሪስት መስህቦች ልማት ከተካሄደባችው መካከልም የዓለም አቀፍ ቅርስ በሆነው ጀጎልን ጨምሮ ሌሎች የኮሪደርና የመስህብ ስፍራዎችን የመንከባከብ፣ የመጠበቅና የማስዋብ እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ለጎብኚዎቹ ቁጥር መጨመር ጉልህ ሚና ማበርከታቸውን አመልክተዋል።
እንዲሁም በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ድርጅት(ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የሸዋል ኢድ በዓል አከባበርም ለጎብኚዎች ቁጥር መጨመር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።

በሐረሪ ክልል በቱሪስቶች ከሚጎበኙት ቅርሶች መካከል የዓለም ቅርስ የሆነው የጀጎል ግንብ፣ በውስጡ የሚገኙ ጥንታዊ መኖሪያ ቤቶችና አምስቱ የጀጎል ግንብ መግቢያ በሮች ይገኙበታል።
በተጨማሪም ባህላዊ የዕደ ጥበብ ውጤቶች፣ የፈረንሳዊው ባለቅኔ አርተር ራንቦ መኖሪያ ቤት፣ የሐረሪ ብሔረሰብ ሙዚየሞች፣ አድባራት፣ የጅብ ምገባ ትርኢትና ሌሎችም በቱሪስቶች የሚገበኙ ጥንታዊ፣ ሃይማኖታዊና ታሪካዊ የመስህብ ስፍራዎች ናቸው።
በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት የክልሉን የመስህብ ስፍራዎችን 7ሺህ 877 የውጭ ቱሪስቶች ጎብኝተዋል ያሉት ሃላፊው፤ ይህም ከዓምናው ጋር ሲነጻጸር በ31 ነጥብ 6 በመቶ ብልጫ እንዳለው ነው የገለጹት።
በተጨማሪም ከ123ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች በክልሉ የሚገኙ የመስህብ ስፍራዎችን መጎብኘታቸውን ገልፀው፤ ይህም ከዓምናው በ7 ነጥብ 4 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን አክለዋል።
ከዚህ ጎን ለጎን የተከናወነው የኮሪደር ልማት ግንባታና የማስዋብ ሥራዎቹ ከተማውን ለቱሪስቶች ምቹና ውብ እንዲሆን ማስቻላቸውንም አቶ ተወለዳ ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025