የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በሐረሪ ክልል የኮሪደርና የቱሪስት መስህብ ስፍራ ልማቶች የጎብኚዎችን ቁጥር እንዲጨምር አስችሏል

Apr 15, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የኮሪደርና የቱሪስት መስህብ ልማቶች የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር ማድረጉን የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ቅርስ ቢሮ አስታወቀ፡፡

በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የክልሉን የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች ከጎበኙ ከ130ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ከ136 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱም ተገልጿል።


የቢሮው ሃላፊ አቶ ተወለዳ አብዶሽ እንደገለጹት ቢሮው የክልሉ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን በማስተዋወቅና በማልማት የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር አድርጓል።

የቱሪስት መስህቦች ልማት ከተካሄደባችው መካከልም የዓለም አቀፍ ቅርስ በሆነው ጀጎልን ጨምሮ ሌሎች የኮሪደርና የመስህብ ስፍራዎችን የመንከባከብ፣ የመጠበቅና የማስዋብ እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ለጎብኚዎቹ ቁጥር መጨመር ጉልህ ሚና ማበርከታቸውን አመልክተዋል።

እንዲሁም በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ድርጅት(ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የሸዋል ኢድ በዓል አከባበርም ለጎብኚዎች ቁጥር መጨመር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።


በሐረሪ ክልል በቱሪስቶች ከሚጎበኙት ቅርሶች መካከል የዓለም ቅርስ የሆነው የጀጎል ግንብ፣ በውስጡ የሚገኙ ጥንታዊ መኖሪያ ቤቶችና አምስቱ የጀጎል ግንብ መግቢያ በሮች ይገኙበታል።

በተጨማሪም ባህላዊ የዕደ ጥበብ ውጤቶች፣ የፈረንሳዊው ባለቅኔ አርተር ራንቦ መኖሪያ ቤት፣ የሐረሪ ብሔረሰብ ሙዚየሞች፣ አድባራት፣ የጅብ ምገባ ትርኢትና ሌሎችም በቱሪስቶች የሚገበኙ ጥንታዊ፣ ሃይማኖታዊና ታሪካዊ የመስህብ ስፍራዎች ናቸው።

በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት የክልሉን የመስህብ ስፍራዎችን 7ሺህ 877 የውጭ ቱሪስቶች ጎብኝተዋል ያሉት ሃላፊው፤ ይህም ከዓምናው ጋር ሲነጻጸር በ31 ነጥብ 6 በመቶ ብልጫ እንዳለው ነው የገለጹት።

በተጨማሪም ከ123ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች በክልሉ የሚገኙ የመስህብ ስፍራዎችን መጎብኘታቸውን ገልፀው፤ ይህም ከዓምናው በ7 ነጥብ 4 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን አክለዋል።

ከዚህ ጎን ለጎን የተከናወነው የኮሪደር ልማት ግንባታና የማስዋብ ሥራዎቹ ከተማውን ለቱሪስቶች ምቹና ውብ እንዲሆን ማስቻላቸውንም አቶ ተወለዳ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026