
አዲስ አበባ ፤ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የአስተዳደር ዘርፍ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ርዕሰ መስተዳድር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።

የክልሉ ርዕሰ መስተደድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ርኢ/ር) በክልሉ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በሀብት ብክነት፣ ከልማት ሥራዎች ውጤታማነት ችግር ጋር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በተቀናጀ መልኩ መፍታት እንደሚገባ ገልጸዋል።
በክልሉ ሰላም እና ፀጥታ፣ተቋማት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።
ወንጀል፣ሙስና እና ብልሹ አሰራር እንዲሁም ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን መከላከል የተለየ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።
እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፤ ከህዝቡ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመቀበል የሚባክን የመንግስት በጀት ማዳንና የህግን የማስከበር ሥራ ማከናወን ይገባል።
የባህል ፍርድ ቤቶች ማጠናከር እና የፍትህ ትራንስፎርሜሽን ስራ ማፋጠን እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ በመንግሥት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆን በቴክኖሎጂ መደገፍ እና ህዝብን ከማገልገል አንጻር ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባልም ነው ያሉት።
በክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ወቅታዊ እና ሚዛናዊነቱን የጠበቀ መረጃዎችን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች መጠናከር እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በክልሉ የመንግሥት የልማት ሥራዎችን የሚያደናቅፉ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በተቀናጀ መልኩ መፍታት እንደሚጠበቅም መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025