የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው-ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር)

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የአስተዳደር ዘርፍ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ርዕሰ መስተዳድር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።


የክልሉ ርዕሰ መስተደድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ርኢ/ር) በክልሉ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በሀብት ብክነት፣ ከልማት ሥራዎች ውጤታማነት ችግር ጋር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በተቀናጀ መልኩ መፍታት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በክልሉ ሰላም እና ፀጥታ፣ተቋማት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

ወንጀል፣ሙስና እና ብልሹ አሰራር እንዲሁም ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን መከላከል የተለየ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።

እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፤ ከህዝቡ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመቀበል የሚባክን የመንግስት በጀት ማዳንና የህግን የማስከበር ሥራ ማከናወን ይገባል።

የባህል ፍርድ ቤቶች ማጠናከር እና የፍትህ ትራንስፎርሜሽን ስራ ማፋጠን እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

በሌላ በኩል በክልሉ በመንግሥት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆን በቴክኖሎጂ መደገፍ እና ህዝብን ከማገልገል አንጻር ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባልም ነው ያሉት።

በክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ወቅታዊ እና ሚዛናዊነቱን የጠበቀ መረጃዎችን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች መጠናከር እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በክልሉ የመንግሥት የልማት ሥራዎችን የሚያደናቅፉ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በተቀናጀ መልኩ መፍታት እንደሚጠበቅም መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025