የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው-ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር)

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የአስተዳደር ዘርፍ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ርዕሰ መስተዳድር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።


የክልሉ ርዕሰ መስተደድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ርኢ/ር) በክልሉ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በሀብት ብክነት፣ ከልማት ሥራዎች ውጤታማነት ችግር ጋር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በተቀናጀ መልኩ መፍታት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በክልሉ ሰላም እና ፀጥታ፣ተቋማት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

ወንጀል፣ሙስና እና ብልሹ አሰራር እንዲሁም ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን መከላከል የተለየ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።

እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፤ ከህዝቡ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመቀበል የሚባክን የመንግስት በጀት ማዳንና የህግን የማስከበር ሥራ ማከናወን ይገባል።

የባህል ፍርድ ቤቶች ማጠናከር እና የፍትህ ትራንስፎርሜሽን ስራ ማፋጠን እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

በሌላ በኩል በክልሉ በመንግሥት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆን በቴክኖሎጂ መደገፍ እና ህዝብን ከማገልገል አንጻር ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባልም ነው ያሉት።

በክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ወቅታዊ እና ሚዛናዊነቱን የጠበቀ መረጃዎችን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች መጠናከር እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በክልሉ የመንግሥት የልማት ሥራዎችን የሚያደናቅፉ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በተቀናጀ መልኩ መፍታት እንደሚጠበቅም መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026