አዲስ አበባ ፤ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የአስተዳደር ዘርፍ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ርዕሰ መስተዳድር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።
የክልሉ ርዕሰ መስተደድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ርኢ/ር) በክልሉ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በሀብት ብክነት፣ ከልማት ሥራዎች ውጤታማነት ችግር ጋር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በተቀናጀ መልኩ መፍታት እንደሚገባ ገልጸዋል።
በክልሉ ሰላም እና ፀጥታ፣ተቋማት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።
ወንጀል፣ሙስና እና ብልሹ አሰራር እንዲሁም ህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን መከላከል የተለየ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።
እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፤ ከህዝቡ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመቀበል የሚባክን የመንግስት በጀት ማዳንና የህግን የማስከበር ሥራ ማከናወን ይገባል።
የባህል ፍርድ ቤቶች ማጠናከር እና የፍትህ ትራንስፎርሜሽን ስራ ማፋጠን እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ በመንግሥት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆን በቴክኖሎጂ መደገፍ እና ህዝብን ከማገልገል አንጻር ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባልም ነው ያሉት።
በክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ወቅታዊ እና ሚዛናዊነቱን የጠበቀ መረጃዎችን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች መጠናከር እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በክልሉ የመንግሥት የልማት ሥራዎችን የሚያደናቅፉ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በተቀናጀ መልኩ መፍታት እንደሚጠበቅም መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025