አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በየዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን በላቀ ውጤት ለማስቀጠል በጊዜ የለንም መንፈስ በትጋት መስራት እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ እና የዘርፎች ዕቅድ አፈጻጸምን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ከፌዴራል ተቋማት የስራ ኃላፊዎች ጋር መገምገም ተጀምሯል፡፡
በመድረኩ በ100 ቀናት የትኩረት ማዕከል የሆኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ የተገኙ ውጤቶች፣ የታዩ ክፍተቶች እና የትኩረት አቅጣጫዎች ከተቋማቱ የስራ ኃላፊዎች ጋር በጋራ እንደሚታዩ ይጠበቃል፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ እና በተለያዩ መስኮች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል።
በየዘርፉ የተሰሩ ስራዎችን በአግባቡ መለካት፣ ማቅረብ እንዲሁም ለሌላው ማስረዳት እንደሚገባ ገልጸው፤ አሁንም አመራሩ በጊዜ የለኝም መንፈስ መስራት እንዳለበት ተናግረዋል።
ሰራተኛውን በአግባቡ የማይመራ፣ የማይመዝን እና የማይከታተል መኖሩንና በጥቂት ታታሪ ሰራተኞችና ኃላፊዎች ተቋማት የሚንቀሳቀሱበት ሁኔታ እንደሚስተዋል ገልጸው፤ ይህንን መፈተሽ እና ማስተካከል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከታሰበው በላይ የተሳኩ ድሎች መመዝገባቸውን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አሁንም ትኩረት የሚፈልጉ አካባቢዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
አገራዊና ዓለም አቀፋዊ አውድን በመገንዘብ እየተገኙ ያሉ ስኬቶችን ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸው የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል ከዚህ በላይ መሮጥ እንደሚገባ አመልክተዋል።
የተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ እና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርምን መፈጸም ውዴታ ሳይሆን ግዴታ መሆኑንም ተናግረዋል።
አገልግሎት አሰጣጥ ሁሉንም ሊያሳስብ የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው፤ በጠንካራ አመራር እና ሰራተኛ የታጀበ አገልግሎት አሰጣጥ መኖር እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በቀጣዮቹ ሶስት ወራት ከተገኙ ውጤቶች በላይ ለማሳካት ሁሉም በጊዜ የለኝም መንፈስ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025