
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 13/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ የአህጉሪቷ ድምጽ ጎልቶ እንዲሰማ ለማድረግ በጋራ እንደሚሰሩ አስታወቁ።
ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያ የሚዘጋጀው ጉባኤ በስኬት ለማዘጋጀት እያከናወኑ የሚገኙትን ስራ የሚገመግም ስብሰባ አድርገዋል።
በውይይቱ ኢትዮጵያ እና ኮሚሽኑ ለጉባኤው እያደረጉት ያለው ስትራቴጂካዊ ዝግጅት ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለአህጉሪቷ የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች ዘላቂ መፍትሄ የሚያበጅ ሆኖ ሁነት እንዲሆን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ የፕላን እና ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በጉባኤው ትርጉም ያለው ውጤት እና ለውጥ የሚፈጥር ውይይት እንዲካሄድ በጋራ እየሰሩ ይገኛሉ።
ጉባኤው የአፍሪካ ድምጽ ጎልቶ እንዲሰማ እና በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የማይበገር አቅም መገንባት እና ዘላቂ ልማት የሚያረጋግጥ ስትራቴጂ መቅረጽ የሚያስችል መድረክ መፍጠር ላይ ትኩረት ማድረጉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያሳያል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026