
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 13/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ የአህጉሪቷ ድምጽ ጎልቶ እንዲሰማ ለማድረግ በጋራ እንደሚሰሩ አስታወቁ።
ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያ የሚዘጋጀው ጉባኤ በስኬት ለማዘጋጀት እያከናወኑ የሚገኙትን ስራ የሚገመግም ስብሰባ አድርገዋል።
በውይይቱ ኢትዮጵያ እና ኮሚሽኑ ለጉባኤው እያደረጉት ያለው ስትራቴጂካዊ ዝግጅት ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለአህጉሪቷ የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች ዘላቂ መፍትሄ የሚያበጅ ሆኖ ሁነት እንዲሆን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ የፕላን እና ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በጉባኤው ትርጉም ያለው ውጤት እና ለውጥ የሚፈጥር ውይይት እንዲካሄድ በጋራ እየሰሩ ይገኛሉ።
ጉባኤው የአፍሪካ ድምጽ ጎልቶ እንዲሰማ እና በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የማይበገር አቅም መገንባት እና ዘላቂ ልማት የሚያረጋግጥ ስትራቴጂ መቅረጽ የሚያስችል መድረክ መፍጠር ላይ ትኩረት ማድረጉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያሳያል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026