የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤው የአፍሪካ ድምጽ ጎልቶ እንዲሰማ በጋራ እንደሚሰሩ ገለጹ

Apr 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 13/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ የአህጉሪቷ ድምጽ ጎልቶ እንዲሰማ ለማድረግ በጋራ እንደሚሰሩ አስታወቁ።

ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያ የሚዘጋጀው ጉባኤ በስኬት ለማዘጋጀት እያከናወኑ የሚገኙትን ስራ የሚገመግም ስብሰባ አድርገዋል።

በውይይቱ ኢትዮጵያ እና ኮሚሽኑ ለጉባኤው እያደረጉት ያለው ስትራቴጂካዊ ዝግጅት ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል።

ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለአህጉሪቷ የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች ዘላቂ መፍትሄ የሚያበጅ ሆኖ ሁነት እንዲሆን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ የፕላን እና ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በጉባኤው ትርጉም ያለው ውጤት እና ለውጥ የሚፈጥር ውይይት እንዲካሄድ በጋራ እየሰሩ ይገኛሉ።

ጉባኤው የአፍሪካ ድምጽ ጎልቶ እንዲሰማ እና በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የማይበገር አቅም መገንባት እና ዘላቂ ልማት የሚያረጋግጥ ስትራቴጂ መቅረጽ የሚያስችል መድረክ መፍጠር ላይ ትኩረት ማድረጉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያሳያል።

ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026