የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የክልሉን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው

Apr 23, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የክልሉን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።


ሚኒስትሩ በአሶሳ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።


በእዚህ ወቅት እንደገለፁት፥ በክልሉ በመከናወን ላይ ያሉ የልማት ሥራዎች የክልሉን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው።


በሌማት ትሩፋት መርሀግብር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰው፥ልማቱን በመደገፍና በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባል።


በተለይ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች አበረታች በመሆናቸው የእንስሳት ተዋፅኦ ምርታማነት እንዲጨምር የራሱ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።


በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትም የከተማዋን የወደፊት ዕድገት ታሳቢ ያደረገ እና ለኢንቨስትመንት ምቹ እንድትሆን የሚያደርግ መሆኑንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።


በተጨማሪም ልማቱ ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጋር ተያይዞ የቱሪዝም ፍሰት እንዲጨምር ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰው፥የልማት ስራዎቹ የክልሉን እድገት ከማፋጠን ባለፈ ህዝብን ተጠቃሚ ያደርጋሉ ብለዋል።


ሚኒስትሩ በተጨማሪም በአሶሳ ከተማ በ469 ሚሊዮን ብር እየተገነባ ያለውን የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ግንባታ ማዕከል ጎብኝተዋል።


ማዕከሉ ፈሳሽ ቆሻሻን በማጣራት ለልማት ሥራ ለማዋል እና ዘመናዊ የቆሻሻ አወገጋድ ስርዓት እንዲፈጠር ያግዛል ብለዋል።


ይህም አሶሳ ከተማን ጽዱ እና ውብ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ያግዛል ሲሉ አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025