
አሶሳ፤ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የክልሉን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በአሶሳ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።
በእዚህ ወቅት እንደገለፁት፥ በክልሉ በመከናወን ላይ ያሉ የልማት ሥራዎች የክልሉን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው።
በሌማት ትሩፋት መርሀግብር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰው፥ልማቱን በመደገፍና በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባል።
በተለይ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች አበረታች በመሆናቸው የእንስሳት ተዋፅኦ ምርታማነት እንዲጨምር የራሱ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትም የከተማዋን የወደፊት ዕድገት ታሳቢ ያደረገ እና ለኢንቨስትመንት ምቹ እንድትሆን የሚያደርግ መሆኑንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ልማቱ ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጋር ተያይዞ የቱሪዝም ፍሰት እንዲጨምር ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰው፥የልማት ስራዎቹ የክልሉን እድገት ከማፋጠን ባለፈ ህዝብን ተጠቃሚ ያደርጋሉ ብለዋል።
ሚኒስትሩ በተጨማሪም በአሶሳ ከተማ በ469 ሚሊዮን ብር እየተገነባ ያለውን የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ግንባታ ማዕከል ጎብኝተዋል።
ማዕከሉ ፈሳሽ ቆሻሻን በማጣራት ለልማት ሥራ ለማዋል እና ዘመናዊ የቆሻሻ አወገጋድ ስርዓት እንዲፈጠር ያግዛል ብለዋል።
ይህም አሶሳ ከተማን ጽዱ እና ውብ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ያግዛል ሲሉ አክለዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025