የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የክልሉን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው

Apr 23, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የክልሉን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።


ሚኒስትሩ በአሶሳ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።


በእዚህ ወቅት እንደገለፁት፥ በክልሉ በመከናወን ላይ ያሉ የልማት ሥራዎች የክልሉን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው።


በሌማት ትሩፋት መርሀግብር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰው፥ልማቱን በመደገፍና በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባል።


በተለይ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች አበረታች በመሆናቸው የእንስሳት ተዋፅኦ ምርታማነት እንዲጨምር የራሱ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።


በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትም የከተማዋን የወደፊት ዕድገት ታሳቢ ያደረገ እና ለኢንቨስትመንት ምቹ እንድትሆን የሚያደርግ መሆኑንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።


በተጨማሪም ልማቱ ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጋር ተያይዞ የቱሪዝም ፍሰት እንዲጨምር ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰው፥የልማት ስራዎቹ የክልሉን እድገት ከማፋጠን ባለፈ ህዝብን ተጠቃሚ ያደርጋሉ ብለዋል።


ሚኒስትሩ በተጨማሪም በአሶሳ ከተማ በ469 ሚሊዮን ብር እየተገነባ ያለውን የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ግንባታ ማዕከል ጎብኝተዋል።


ማዕከሉ ፈሳሽ ቆሻሻን በማጣራት ለልማት ሥራ ለማዋል እና ዘመናዊ የቆሻሻ አወገጋድ ስርዓት እንዲፈጠር ያግዛል ብለዋል።


ይህም አሶሳ ከተማን ጽዱ እና ውብ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ያግዛል ሲሉ አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026