የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተከናወኑ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል

Apr 23, 2025

IDOPRESS

ሐረር፣ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ለውጦች መመዝገባቸው ተገለፀ።


በክልሉ እየተካሄደ በሚገኘው የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ የክልሉ የግብርና ልማት ቢሮና የክልሉ ባህል፣ ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ ሪፖርቶች ቀርበዋል።


ምክትል ርዕሰ መስተደድር እና የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ዑመር በወቅቱ እንዳሉት፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በዘርፉ የተከናወኑ ተግባራት በገጠርና በከተማ የሚገኘውን ህብረተሰብ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እያሸጋገሩ ይገኛሉ።


በሌማት ትሩፋት፣በከተማ ግብርና፣በመስኖ ልማት፣በመኸርና በበልግ ወራት የተሰሩ ስራዎች በሁለት ወረዳዎች የሚገኙ ከ1 ሺህ 800 በላይ ቤተሰቦችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እንዲሸጋገሩ ማድረጉን አንስተዋል።


በዘንድሮ በጋ ወራት 4 ሺህ 600 ሄክታር መሬትን በመስኖ በማልማት ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአዝርዕት፣ የፍራፍሬና አትክልት ምርቶች ሊሰበሰብ መቻሉን ገልጸዋል።


በተለይ በገጠርና በከተማ በዓመት ሶስት ጊዜ የማምረት ባህልን ለማጎልበት የተሰሩ ህዝባዊ ንቅናቄዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እያመጡ መሆኑን አመልክተዋል።


ለአብነትም ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ማሽላን በመስኖ ማምረት እንደሚቻል በሰርቶ ማሳያ በማሳየት በክልሉ ገጠር አካባቢ የሚኖረው ህብረተሰብ ስራውን ወደ ተግባር ለመቀየር ዝግጁ እንዲሆን መደረጉንም አስረድተዋል።


ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተሰሩ ስራዎች ምርትና ምርታማነት እንዲጨምርና ከተረጂነት መላቀቅ እንደሚቻል ያሳዩ ተጨባጭ ውጤቶች የተመዘገበባቸው መሆናቸውን ወይዘሮ ሮዛ ተናግረዋል።


በበጋ ወራት የተመረቱ የቲማቲም፣ የቃሪያ እና የሽንኩርት ምርቶች ለቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ቀርበው ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ዓይነተኛ ሚና መጫወታቸውን ገልፀዋል።


በቀሪ በጀት ወራት የተገኙ ውጤቶችን ከማጠናከር በተጨማሪ ለቀጣይ የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ የችግኝ ዝግጅት ስራን የማጠናቀቅ እና የማዳበሪያ አቅርቦትን የማፋጠን ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።


የክልሉ የባህል፣ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወለዳ አብዶሽ፤ ከ130 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ አገራት ቱሪስቶች የክልሉን የቱሪዝም ሃብቶች መጎብኘታቸውን ገልጸዋል።


ከእነዚህ መካከል 123 ሺህ የሀገር ውስጥ ሲሆኑ ቀሪዎቹ የተለያዩ አገራት ቱሪስቶች መሆናቸውን አንስተው በዚህም 14 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል።


ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ30 በመቶ እድገት ማሳየቱን ገልጸው በክልሉ ቱሪዝም ጥሩ የሃብት ምንጭ እየሆነ መምጣቱንም ገልፀዋል።


በተለይም የኮሪደር ልማት ክንውኑ ከተማዋን ውብና ለቱሪስቶች ምቹ ያደረጋት መሆኑን ጠቅሰው ታሪካዊ መስህቦችና ሌሎች የክልሉ እምቅ የቱሪዝም ሃብቶች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025