የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የቡና ጥራትን በማሻሻል የዘርፉን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Apr 24, 2025

IDOPRESS

ጅማ፣ሚያዝያ15/2017(ኢዜአ)፡- የቡና ጥራትን በማሻሻል ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግና የአምራቹን ተጠቃሚነት ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።

አርሶአደር ተኮር ጥራቱን የጠበቀ የስፔሻሊቲ ቡና አዘገጃጀት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በጅማ ከተማ እየተሰጠ ነው።

የባለስልጣኑ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ታጋይ ኑሩ እንደገለጹት የቡና ጥራትና ደረጃ በማሳደግ ከዘርፉ የሚገኘውን የገቢ መጠን ለማሳደግና የቡና አምራቹን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ።

በቡና ጥራት የማይደራደር አርሶአደር ለመፍጠር የቡና ጥራት ንቅናቄ ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰዋል ።

“በሁሉም የቡና አምራች አካባቢዎች የቡና ጥራትና ጣእም ተቀባይነትን የሚያረጋግጡ ስራዎችን መተግበር ያስፈልጋል” ብለዋል።

“ጥራቱን የጠበቀ ቡናን ለማዘጋጀት ከተለመደው የተለየ አሰራር መተግበርና በትኩረት መከታተል ያስፈልጋል” ያሉት አቶ ታጋይ ጥራት በገበያው ላይ ከፍተኛ ሚና እንዳለው አስታውቀዋል ።

የጅማ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አወል ከሊል በበኩላቸው “የዞኑን የቡና ምርት ጥራት ደረጃን ለማሻሻል በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው” ብለዋል።

በዞኑ የሚመረተው ቡና በማእከላዊና በዓለም ገበያ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን የእፔሻሊቲ ቡና ጥራት ላይ በልዩ ትኩረት እንዲሰራ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የሚተገበር መሆኑን አመልክተዋል ።

ቡና አምራች አርሶ አደሮችን፣ ነጋዴዎችና ባለሞያዎችን እንዲሁም የማጠቢያና መፈልፈያ ኢንዱስትሪ ባለሙያዎችን ያሳተፈ ውይይት መደረጉን አስታውቀዋል ።

“ስልጠናው በቡና ጥራት የታዩ ጉድለቶችን ለማረምና ጥራቱ ላይ ትኩረት እንድናደርግ የሚያግዝ ነው “ ያሉት ደግሞ ቡና አምራች አርሶአደር ሙስጠፋ መሀመድ ናቸው ።

ሌላው አርሶ አደር ሙስጠፋ አባ ቀኖ በበኩላቸው “ቡና በምርት ስብሰባ ወቅት፣ በመጋዘን ቆይታውና በማጓጓዝ ወቅት ሊበላሽ የሚችል በመሆኑ የግንዛቤ ስልጠናው በስፋት መሰጠት አለበት” ብለዋል።

በስልጠናው ላይ ከኦሮሚያ ክልል ከጅማ፣ ኢሉ አባቦርና ቡኖ በደሌ ዞኖች እንዲሁም ከደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከካፋና ከቤንች ሸኮ ዞኖች የተውጣጡ አምራቾችና ባለሞያዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026