ጅማ፣ሚያዝያ15/2017(ኢዜአ)፡- የቡና ጥራትን በማሻሻል ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግና የአምራቹን ተጠቃሚነት ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።
አርሶአደር ተኮር ጥራቱን የጠበቀ የስፔሻሊቲ ቡና አዘገጃጀት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በጅማ ከተማ እየተሰጠ ነው።
የባለስልጣኑ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ታጋይ ኑሩ እንደገለጹት የቡና ጥራትና ደረጃ በማሳደግ ከዘርፉ የሚገኘውን የገቢ መጠን ለማሳደግና የቡና አምራቹን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ።
በቡና ጥራት የማይደራደር አርሶአደር ለመፍጠር የቡና ጥራት ንቅናቄ ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰዋል ።
“በሁሉም የቡና አምራች አካባቢዎች የቡና ጥራትና ጣእም ተቀባይነትን የሚያረጋግጡ ስራዎችን መተግበር ያስፈልጋል” ብለዋል።
“ጥራቱን የጠበቀ ቡናን ለማዘጋጀት ከተለመደው የተለየ አሰራር መተግበርና በትኩረት መከታተል ያስፈልጋል” ያሉት አቶ ታጋይ ጥራት በገበያው ላይ ከፍተኛ ሚና እንዳለው አስታውቀዋል ።
የጅማ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አወል ከሊል በበኩላቸው “የዞኑን የቡና ምርት ጥራት ደረጃን ለማሻሻል በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው” ብለዋል።
በዞኑ የሚመረተው ቡና በማእከላዊና በዓለም ገበያ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን የእፔሻሊቲ ቡና ጥራት ላይ በልዩ ትኩረት እንዲሰራ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የሚተገበር መሆኑን አመልክተዋል ።
ቡና አምራች አርሶ አደሮችን፣ ነጋዴዎችና ባለሞያዎችን እንዲሁም የማጠቢያና መፈልፈያ ኢንዱስትሪ ባለሙያዎችን ያሳተፈ ውይይት መደረጉን አስታውቀዋል ።
“ስልጠናው በቡና ጥራት የታዩ ጉድለቶችን ለማረምና ጥራቱ ላይ ትኩረት እንድናደርግ የሚያግዝ ነው “ ያሉት ደግሞ ቡና አምራች አርሶአደር ሙስጠፋ መሀመድ ናቸው ።
ሌላው አርሶ አደር ሙስጠፋ አባ ቀኖ በበኩላቸው “ቡና በምርት ስብሰባ ወቅት፣ በመጋዘን ቆይታውና በማጓጓዝ ወቅት ሊበላሽ የሚችል በመሆኑ የግንዛቤ ስልጠናው በስፋት መሰጠት አለበት” ብለዋል።
በስልጠናው ላይ ከኦሮሚያ ክልል ከጅማ፣ ኢሉ አባቦርና ቡኖ በደሌ ዞኖች እንዲሁም ከደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከካፋና ከቤንች ሸኮ ዞኖች የተውጣጡ አምራቾችና ባለሞያዎች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025