የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የፌዴራል መንግስት ተቋማት የኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ሙያተኞች የመዲናዋን የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው

Apr 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2017(ኢዜአ)፦ የፌዴራል መንግስት ተቋማት የኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ሙያተኞች በአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችን በመጎብኘት ላይ ይገኛሉ።

የስራ ኃላፊዎቹና ሙያተኞቹ መነሻቸውን ካዛንችስ ኮሪደር ልማት በማድረግ በተለያዩ የመዲናዋ አካባቢዎች የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው እንደሚጎበኙ ተገልጿል።

ጉብኝቱን አስመልክቶ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምፀሀይ ጳውሎስ ገለፃ አድርገዋል።


በገለፃቸውም፥ የኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ሙያተኞች ጉብኝት በኢኮኖሚው መስክ እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን በተግባር እንዲመለከቱ ነው ብለዋል።

እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የቀጣዩን ትውልድ መፂኢ እጣ ፋንታ ታሳቢ በማድረግ ተሻጋሪ እሳቤ ተግባራዊ የተደረገባቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ በበኩላቸው በመዲናዋ የተከናወኑ የኮሪደርና መልሶ ማልማት ስራዎች የከተማዋን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ከማሳደግ ባለፈ በተጎሳቆለ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ የቀየረ ነው ብለዋል።

በሂደቱም ቅርሶችን በመጠበቅ ለትውልድ የሚሻገሩ ስኬታማ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች የተከናወኑበት መሆኑንም አንስተዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በኮሪደር የለሙ ፕሮጀክቶች ክትትል ኃላፊ አቶ ከድር አደም፥ በመዲናዋ የተገነቡ የመሰረተ ልማቶች የተቀናጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በከተማዋ የኮሪደር፣ የወንዞች ዳርቻ እና መልሶ ማልማት ስራዎችን ታሳቢ በማድረግ አሳታፊና አካታች እንዲሁም ጥራትና ፍጥነትን መርህ በማድረግ የተሰሩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025