የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የፌዴራል መንግስት ተቋማት የኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ሙያተኞች የመዲናዋን የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው

Apr 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2017(ኢዜአ)፦ የፌዴራል መንግስት ተቋማት የኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ሙያተኞች በአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችን በመጎብኘት ላይ ይገኛሉ።

የስራ ኃላፊዎቹና ሙያተኞቹ መነሻቸውን ካዛንችስ ኮሪደር ልማት በማድረግ በተለያዩ የመዲናዋ አካባቢዎች የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው እንደሚጎበኙ ተገልጿል።

ጉብኝቱን አስመልክቶ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምፀሀይ ጳውሎስ ገለፃ አድርገዋል።


በገለፃቸውም፥ የኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ሙያተኞች ጉብኝት በኢኮኖሚው መስክ እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን በተግባር እንዲመለከቱ ነው ብለዋል።

እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የቀጣዩን ትውልድ መፂኢ እጣ ፋንታ ታሳቢ በማድረግ ተሻጋሪ እሳቤ ተግባራዊ የተደረገባቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ በበኩላቸው በመዲናዋ የተከናወኑ የኮሪደርና መልሶ ማልማት ስራዎች የከተማዋን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ከማሳደግ ባለፈ በተጎሳቆለ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ የቀየረ ነው ብለዋል።

በሂደቱም ቅርሶችን በመጠበቅ ለትውልድ የሚሻገሩ ስኬታማ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች የተከናወኑበት መሆኑንም አንስተዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በኮሪደር የለሙ ፕሮጀክቶች ክትትል ኃላፊ አቶ ከድር አደም፥ በመዲናዋ የተገነቡ የመሰረተ ልማቶች የተቀናጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በከተማዋ የኮሪደር፣ የወንዞች ዳርቻ እና መልሶ ማልማት ስራዎችን ታሳቢ በማድረግ አሳታፊና አካታች እንዲሁም ጥራትና ፍጥነትን መርህ በማድረግ የተሰሩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026