
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ ወጥነት ያለው ጥራት በሁሉም የግብርና ምርቶች ላይ ልናሳይ ይገባል ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ተናገሩ።
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጥራት ምርመራ ማዕከል አክሪዲቴሽን ትውውቅና የሰርቲፍኬት ርክክብ ፕሮግራም ተካሂዷል።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የምግብ ዋስትናና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምርቶችን መተካት እና ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚውሉ በብዛትና በጥራት ማምረት ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን በብዛት ከማምረት ጎን ለጎን ጥራቱን ማረጋገጥ እንደሚገባም ገልጸዋል።
ቀደም ሲል የነበረው የግብርና ፖሊሲ ማምረት ላይ እንጂ ጥራትን ታሳቢ ያላደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ ወጥነት ያለው ጥራት በሁሉም የግብርና ምርቶች ላይ ልናሳይ ይገባል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ያለው የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጥራት ምርመራ የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጤንነት የሚያረጋገጥ አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህ ተሞክሮ በእጽዋትና በሁሉም ዘርፍ በቀጣይነት ማስፋፋት ይገባል በማለትም አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ፤ ባለስልጣኑ የግብርና ምርትና ግብዓት ጥራትና ደህንነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ የጥራት መስፈርቶችን፣ ህጋዊ ማዕቀፎችንና የቴክኖሎጂ አሰራሮችን በመዘርጋት ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
በባለስልጣኑ ደረጃቸውን የጠበቁ የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጥራት ደህንነት ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ 13 የምርመራ ላቦራቶሪዎች በሶስተኛ ወገን እውቅና ማግኘቱን ገልጸዋል።
ይህም የግብርና ምርትና ግብዓት ቁጥጥር ደረጃን የሚያሳድግ መሆኑን በመግለጽ፡፡
የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ቦንሳ ባይሳ በበኩላቸው፤ አክሪዲቴሽን ተቋማት የተሻለ አሰራር ሥርዓት እንዲከተሉ፣ ሂደታቸውን ያለማቋረጥ እንዲያሻሽሉ የሚያበረታታና ተወዳዳሪነታቸውን በሚጨምር መልኩ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በባለስልጣኑ የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጥራት ምርመራ ማዕከል ኃላፊ ዶክተር በላቸው ተፈራ፤ በበኩላቸው ማዕከሉ ባለፉት አስር ዓመታት የዓለም አቀፍ ደረጃውን የተከተለ አደረጃጀት፣ ኬሚካል አጠቃቀምና ምርመራን ተግባራዊ ማድረጉ ለዚህ ውጤት እንዳበቃው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የሚሰጣቸው 66 አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ዲጂታል ማድረጉና ተገልጋዮች ወደ ተቋሙ መምጣት ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ቦታ ሆነው በዲጂታል አማካኝነት አገልግሎቱን እንዲያገኙ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
ለአብነትም እንደ አበባ፣ ቡና፣ ስጋ፣ ተረፈ ስጋ፣ የቁም እንስሳት፣ የእንስሳት መኖ፣ የእንስሳት መድኃኒት ያሉ የወጪና ገቢ ምርቶች ላይ ፍተሻ በማድረግ የመግቢያና መውጫ ፈቃድ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ተመላክቷል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026