የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ወጥነት ያለው ጥራት በሁሉም የግብርና ምርቶች ላይ ልናሳይ ይገባል - ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)

Apr 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ ወጥነት ያለው ጥራት በሁሉም የግብርና ምርቶች ላይ ልናሳይ ይገባል ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ተናገሩ።

የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጥራት ምርመራ ማዕከል አክሪዲቴሽን ትውውቅና የሰርቲፍኬት ርክክብ ፕሮግራም ተካሂዷል።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የምግብ ዋስትናና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምርቶችን መተካት እና ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚውሉ በብዛትና በጥራት ማምረት ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን በብዛት ከማምረት ጎን ለጎን ጥራቱን ማረጋገጥ እንደሚገባም ገልጸዋል።

ቀደም ሲል የነበረው የግብርና ፖሊሲ ማምረት ላይ እንጂ ጥራትን ታሳቢ ያላደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ ወጥነት ያለው ጥራት በሁሉም የግብርና ምርቶች ላይ ልናሳይ ይገባል ብለዋል።

በኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ያለው የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጥራት ምርመራ የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጤንነት የሚያረጋገጥ አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህ ተሞክሮ በእጽዋትና በሁሉም ዘርፍ በቀጣይነት ማስፋፋት ይገባል በማለትም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ፤ ባለስልጣኑ የግብርና ምርትና ግብዓት ጥራትና ደህንነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ የጥራት መስፈርቶችን፣ ህጋዊ ማዕቀፎችንና የቴክኖሎጂ አሰራሮችን በመዘርጋት ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።

በባለስልጣኑ ደረጃቸውን የጠበቁ የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጥራት ደህንነት ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ 13 የምርመራ ላቦራቶሪዎች በሶስተኛ ወገን እውቅና ማግኘቱን ገልጸዋል።

ይህም የግብርና ምርትና ግብዓት ቁጥጥር ደረጃን የሚያሳድግ መሆኑን በመግለጽ፡፡

የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ቦንሳ ባይሳ በበኩላቸው፤ አክሪዲቴሽን ተቋማት የተሻለ አሰራር ሥርዓት እንዲከተሉ፣ ሂደታቸውን ያለማቋረጥ እንዲያሻሽሉ የሚያበረታታና ተወዳዳሪነታቸውን በሚጨምር መልኩ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በባለስልጣኑ የእንስሳት ምርትና ግብዓት ጥራት ምርመራ ማዕከል ኃላፊ ዶክተር በላቸው ተፈራ፤ በበኩላቸው ማዕከሉ ባለፉት አስር ዓመታት የዓለም አቀፍ ደረጃውን የተከተለ አደረጃጀት፣ ኬሚካል አጠቃቀምና ምርመራን ተግባራዊ ማድረጉ ለዚህ ውጤት እንዳበቃው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የሚሰጣቸው 66 አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ዲጂታል ማድረጉና ተገልጋዮች ወደ ተቋሙ መምጣት ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ቦታ ሆነው በዲጂታል አማካኝነት አገልግሎቱን እንዲያገኙ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።

ለአብነትም እንደ አበባ፣ ቡና፣ ስጋ፣ ተረፈ ስጋ፣ የቁም እንስሳት፣ የእንስሳት መኖ፣ የእንስሳት መድኃኒት ያሉ የወጪና ገቢ ምርቶች ላይ ፍተሻ በማድረግ የመግቢያና መውጫ ፈቃድ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025