
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2017(ኢዜአ)፦ የ2017 ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ይገኛል።
የሩጫ ውድድሩን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን ውድድሩም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 4ኛ ዓመት ዝግጅትን አስመልክቶ የተሰናዳ መሆኑ ተገልጿል።
በዝግጅቱ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ታድመዋል።
አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት፤ ውድድሩ የሀገራችንን ምርት ለአለም ለማስተዋወቅ ያለመ ነው ብለዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በበኩላቸው፤ ባለፉት የለውጥ አመታት በተሰሩ ስራዎች ስፖርት ህዝባዊ መሰረት እንዲኖረው ተደርጓል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ ከውጪ ይገቡ የነበሩ የስፖርት ልብሶች ጥራታቸውን ጠብቀው በሀገር ውስጥ መመረት መጀመራቸውን በመግለጽ።
ውድድሩ ባለሃብቶች በስፖርቱ ዘርፍ መዋለ ንዋያቸውን ፈሰስ በማድረግ አስፈላጊ ምርቶችን በማምረት ድጋፍ እንዲያደርጉ እና በሀገር ውስጥ አምራቾች የተመረቱ የስፖርት አልባሳትን ለማስተዋወቅ እንዲሁም አስፈላጊውን የገበያ ትስስር ለመፍጠር መዘጋጀቱ ተገልጿል።
መነሻና መዳረሻውን መስቀል አደባባይ ባደረገው የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በሁለቱም ፆታዎች በቅደም ተከተል ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች የ300ሺህ፣ የ200ሺህ እና የ100ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት የሚበረከትላቸው ይሆናል።
በክለብ ደረጃ በሁለቱም ፆታዎች ተወዳዳሪዎቻቸውን ለሚያሳትፉ ክለቦች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ለሚወጡም እንዲሁ ሽልማት ተዘጋጅቷል።
በውድድሩ የአምራች ኢንዱስትሪ ተዋናዮች፣ አጋር ድርጅቶች፣ ከ34 በላይ የአትሌቲክስ ክለቦችና መላው የአትሌቲክሱ ቤተሰቦች በአጠቃላይ ከ14 ሺህ በላይ ተወዳዳሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026