
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 21/2017(ኢዜአ)፦በተማሪዎች መካከል የሚካሔደው የክህሎት ውድድር ዘርፉን መምራት የሚችል ብቃት ያለው የሰው ሃይል ለማፍራት እንደሚያግዝ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለፁ።
አራተኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር እና 12 ኛው የቱሪዝምና እንግዳ ተቀባይነት ሳምንት ማስጀመርያ መርኃ ግብር እየተከናወነ ይገኛል።
በመርኃ ግብሩ ላይ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ፣ የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ነጋሽ እንዲሁም የቱሪዝም ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በየጊዜው የሚካሔደው የክህሎት ውድድር በዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ሃይል ለማፍራት ትልቅ አቅምን የሚፈጥር ነው።
የክህሎት ውድድሩ የሚሳተፉ ተማሪዎች የተሻለ አቅም ይዘውና ነጥረው እንዲወጡ የሚያግዝ መሆኑንም አንስተዋል።
በተጨማሪም ተማሪዎቹ በሀገር አቀፍ እና በአለም አቀፍ ውድድሮች ላይ የመሳተፍ እድል እንዲኖራቸው ያደርጋል ነው ያሉት።
ተወዳዳሪዎቹ ሀገራቸውን በመወከል በአለም መድረክ እንዲወዳደሩ የሚያስችል እድል እንደሚያስገኝላቸውም ጠቅሰዋል።
የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ነጋሽ በበኩላቸው፤ኢንስቲትዩቱ የቱሪዝም ዘርፉ ክህሎት ባላቸው ዜጎች እንዲመራ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
አራተኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር እና 12ኛው የቱሪዝምና እንግዳ ተቀባይነት ሳምንት "ብሩህ አእምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሀሳብ ከዛሬ ሚያዝያ 21 እና 22 ቀን 2017 ዓም ይካሄዳል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026