የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ዜጎች ከተለያዩ ሀገራት የርቀት ሥራ የሚያገኙበትን እድል እየፈጠረ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 23/2017(ኢዜአ)፦ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ኢትዮጵያውያን በተለያዩ የዓለም ሀገራት የርቀት ስራ የሚያገኙበትን ዕድል እየፈጠረ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዜጎች በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልጸግ፣ ዳታ ሳይንስ እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት እንዲኖራቸው ለማስቻል የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያን ኮደርስ ስልጠና በሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ማስጀመራቸው ይታወቃል፡፡

በዚህም በርካታ ወጣቶች አቅማቸውን ለማሳደግ፣ ተጨማሪ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ዘመኑን የዋጀ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለመሆን ስልጠናውን በኦን ላይን እየተከታተሉ ናቸው፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ለወጣቶች ሥራ ፈጠራ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር እምቅ አቅም አለ፡፡

ይህን አቅም በእውቀትና በክህሎት እንዲመራ በማድረግ ወጣቶች ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ አቅም ታጥቀው ወደ ስራ እንዲገቡ ማስቻል ደግሞ ተጠባቂ እንደሆነ ገልጸዋል።

በዚህም መንግሥት የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ማሰልጠኛ ተቋማትን በብቁ አሰልጣኞችና በመሰረተ ልማት በማበልጸግ ለወጣቶች የሥራ እድል እንዲፈጠር አድርጓል ብለዋል፡፡

የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ማሰልጠኛ ተቋማት በዓመት በአማካኝ እስከ ሦስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ዜጎችን እንደሚያሰለጥኑ ገልጸዋል፡፡

ሚኒስቴሩ በቢዝነስ ልማት መርሃ ግብሩ ወጣቶችን በሥነ ልቦናና ቴክኒክ እያሰለጠነ መሆኑን ገልጸው፤ በተያዘው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ለሦስት ነጥብ አራት ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የውጭ የሥራ ስምሪት ስምምነት መፈራረሟን ገልጸው፤ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ለ344ሺህ ዜጎች የውጭ የሥራ እድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡

የ21ኛ ክፍለ ዘመን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚጠይቀውን ሥርዓተ ትምህርት በመቅረፅ ወጣቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት እንዲኖራቸው እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያን ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም በማላቅ ከተለያዩ ሀገራት የርቀት ሥራ ዕድል እንዲፈጠር አድርጓል ብለዋል፡፡

በስልጠናው የሚሰጡ ኮርሶች ዓለም አቀፍ እውቅና የሚያሰጡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ 45ሺህ ዜጎች በተለያዩ ሀገራት የርቀት ሥራ እንዲያገኙ ማገዙን ተናግረዋል፡፡

ከተለያዩ ሀገራት ኩባንያዎች ተጨማሪ ጥያቄ እየቀረበ መሆኑን ጠቅሰው፤ ወጣቶች ሥራው የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂ አቅም ገንብተው ወደ ሥራ መግባት ይችላሉ ሲሉም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026