
ደሴ፤ ሚያዝያ 23/2017(ኢዜአ)፦ በየዘርፉ ያሉ አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች የሀገርን እድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግ ትልቅ አቅም መሆናቸውን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አህመዲን መሀመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ከሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በኮምቦልቻ ከተማ ሲካሄድ የቆየው 9ኛው የቴክኖሎጂ፣ የክህሎት፣ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር እና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የንግድ ትርዒት እና የደረጃ ሽግግር ሳምንት ተጠናቋል፡፡

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አህመዲን መሀመድ(ዶ/ር)፤ በሁሉም ዘርፎች የሚስተዋሉ አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች የሀገርን እድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግ ትልቅ አቅም የሚፈጥሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሀገርን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ አዳዲስ ፈጠራዎችን ማበርከት፣ የዲጅታል ክንውንና ዘመናዊ አሰራሮችን ማስፋት ይገባል ብለዋል።

በዚህ ረገድ በተለይም የወጣቶችን ፈጠራ ለማሳደግ በመንግስት ድጋፍና ማበረታቻ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የክልሉ መንግስት ተገቢውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አንስተው፤ ሥራና ስልጠና ቢሮ ባካሄደው የፈጠራ፣ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ውድድር ተስፋ ሰጭ ውጤቶች በማየታችን ተደስተናል ብለዋል።
በወጣቶች የቀረቡት የፈጠራ ስራዎች በተለይም ለግብርናው ዘርፍ ትልቅ አቅም የሚሆኑና የአርሶ አደሮችን ድካም የሚቀንሱ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ሥራ እና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የፈጠራ ሥራዎችን በመደገፍና በማበረታታት ለብዙዎች ተደራሽ እንዲሆኑና በስፋት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የተቀናጀ ጥረት ያስፈልጋል ብለዋል።
በተለይ የአርሶ አደሮችን የምርት ጥራት የሚጠብቁ፣ ብክነትን የሚያስቀሩ፣ ጊዜና ጉልበትን የሚቆጥቡ አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች ያሏቸው ወጣቶችን መደገፍና ማበረታታት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026