
ደሴ፤ ሚያዝያ 23/2017(ኢዜአ)፦ በየዘርፉ ያሉ አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች የሀገርን እድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግ ትልቅ አቅም መሆናቸውን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አህመዲን መሀመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ከሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በኮምቦልቻ ከተማ ሲካሄድ የቆየው 9ኛው የቴክኖሎጂ፣ የክህሎት፣ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር እና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የንግድ ትርዒት እና የደረጃ ሽግግር ሳምንት ተጠናቋል፡፡

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አህመዲን መሀመድ(ዶ/ር)፤ በሁሉም ዘርፎች የሚስተዋሉ አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች የሀገርን እድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግ ትልቅ አቅም የሚፈጥሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሀገርን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ አዳዲስ ፈጠራዎችን ማበርከት፣ የዲጅታል ክንውንና ዘመናዊ አሰራሮችን ማስፋት ይገባል ብለዋል።

በዚህ ረገድ በተለይም የወጣቶችን ፈጠራ ለማሳደግ በመንግስት ድጋፍና ማበረታቻ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የክልሉ መንግስት ተገቢውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አንስተው፤ ሥራና ስልጠና ቢሮ ባካሄደው የፈጠራ፣ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ውድድር ተስፋ ሰጭ ውጤቶች በማየታችን ተደስተናል ብለዋል።
በወጣቶች የቀረቡት የፈጠራ ስራዎች በተለይም ለግብርናው ዘርፍ ትልቅ አቅም የሚሆኑና የአርሶ አደሮችን ድካም የሚቀንሱ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ሥራ እና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የፈጠራ ሥራዎችን በመደገፍና በማበረታታት ለብዙዎች ተደራሽ እንዲሆኑና በስፋት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የተቀናጀ ጥረት ያስፈልጋል ብለዋል።
በተለይ የአርሶ አደሮችን የምርት ጥራት የሚጠብቁ፣ ብክነትን የሚያስቀሩ፣ ጊዜና ጉልበትን የሚቆጥቡ አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች ያሏቸው ወጣቶችን መደገፍና ማበረታታት እንደሚገባ ተናግረዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026