አዳማ፤ ሚያዚያ 23/2017(ኢዜአ)፡- የፈጠራና የቴክኖሎጂ ግኝቶች ፈጥነው ወደ ምርት እና አገልግሎት እንዲገቡ በትብብር መስራት እንደሚገባ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።
በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ላለፉት አራት ቀናት በአዳማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ ውድድርና አውደ ርዕይ ተጠናቋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በማጠቃለያ መርሀ ግብሩ እንደገለፁት የክህሎት፣ ፈጠራና ቴክኖሎጂ ውድድርና አውደ ርዕይ እንደሀገር ከድህነት ለመውጣት የሚደረገውን ሂደት የሚደግፍ ነው።
በመሆኑም ክህሎት፣ ልዩ ተሰጥኦና የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ወጣቶች የፈጠራ ውጤቶችን ወደ ምርት እና አገልግሎት ማስገባት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዚህ ሂደት ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ባለፈ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤቶች ለተግባር ሥራ እንዲውሉ የሚጠበቅባቸውን ሊወጡ ይገባል ነው ያሉት።
በክልል ደረጃ በተካሄደው ውድድር የተሻለ እውቀትና ክህሎት ያላቸው ወጣቶች ውጤታማ ሥራ ማቅረባቸውንም ገልጸዋል።
የኦሮሚያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር ኤባ ገርባ በበኩላቸው በክልሉ በክህሎት፣ በቴክኖሎጂና በፈጠራ የበቃ ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
በተለይም ኮሌጆች ቴክኖሎጂን በመቅዳት፣ በማላመድና በማበልፀግ ለልማት እንዲውሉ ማድረግ ላይ የሚጠበቅባቸውን ሚና ለመወጣት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልጸዋል።
ሰሞኑን በአዳማ ከተማ በ22 ክላስተር ሲካሄድ የቆየው ውድድርና አውደ ርዕይ በቴክኖሎጂ፣ ፈጠራና ክህሎት የበቃ ትውልድ ማፍራትን ዓላማ ማድረጉንም አስታውሰዋል።
በውድድሩ የፕላስቲክ ምርቶችን መልሶ መጠቀምና ማጽዳት፣ በግብርና፣ በትራንስፖርት እንዲሁም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት የሚያስችሉ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች መቅረባቸውን ጠቅሰዋል።
እነዚሁ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በተሻለ ደረጃ ለማበልፀግና በስፋት በማምረት ወደ ገበያ እንዲገቡ የክልሉ መንግሥት ዝግጅት እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ለዚህም በቢሾፍቱ፣ ነቀምት፣ አዳማ እና ሻሸመኔ ከተሞች የሚገኙ የቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ ማዕከላት የተመረጡ የፈጠራ ውጤቶችን በስፋት አምርተው ለገበያ እንዲያቀርቡ እየተሰራ መሆኑን አውስተዋል።
በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች የሜዳሊያ፣ የዋንጫ፣ የታብሌትና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025