የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የፈጠራና የቴክኖሎጂ ግኝቶች ፈጥነው ወደ ምርትና አገልግሎት እንዲገቡ በትብብር መስራት ይገባል - የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

May 6, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ሚያዚያ 23/2017(ኢዜአ)፡- የፈጠራና የቴክኖሎጂ ግኝቶች ፈጥነው ወደ ምርት እና አገልግሎት እንዲገቡ በትብብር መስራት እንደሚገባ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።

በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ላለፉት አራት ቀናት በአዳማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ ውድድርና አውደ ርዕይ ተጠናቋል።


የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በማጠቃለያ መርሀ ግብሩ እንደገለፁት የክህሎት፣ ፈጠራና ቴክኖሎጂ ውድድርና አውደ ርዕይ እንደሀገር ከድህነት ለመውጣት የሚደረገውን ሂደት የሚደግፍ ነው።

በመሆኑም ክህሎት፣ ልዩ ተሰጥኦና የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ወጣቶች የፈጠራ ውጤቶችን ወደ ምርት እና አገልግሎት ማስገባት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በዚህ ሂደት ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ባለፈ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤቶች ለተግባር ሥራ እንዲውሉ የሚጠበቅባቸውን ሊወጡ ይገባል ነው ያሉት።

በክልል ደረጃ በተካሄደው ውድድር የተሻለ እውቀትና ክህሎት ያላቸው ወጣቶች ውጤታማ ሥራ ማቅረባቸውንም ገልጸዋል።


የኦሮሚያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር ኤባ ገርባ በበኩላቸው በክልሉ በክህሎት፣ በቴክኖሎጂና በፈጠራ የበቃ ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በተለይም ኮሌጆች ቴክኖሎጂን በመቅዳት፣ በማላመድና በማበልፀግ ለልማት እንዲውሉ ማድረግ ላይ የሚጠበቅባቸውን ሚና ለመወጣት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልጸዋል።

ሰሞኑን በአዳማ ከተማ በ22 ክላስተር ሲካሄድ የቆየው ውድድርና አውደ ርዕይ በቴክኖሎጂ፣ ፈጠራና ክህሎት የበቃ ትውልድ ማፍራትን ዓላማ ማድረጉንም አስታውሰዋል።

በውድድሩ የፕላስቲክ ምርቶችን መልሶ መጠቀምና ማጽዳት፣ በግብርና፣ በትራንስፖርት እንዲሁም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት የሚያስችሉ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች መቅረባቸውን ጠቅሰዋል።

እነዚሁ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በተሻለ ደረጃ ለማበልፀግና በስፋት በማምረት ወደ ገበያ እንዲገቡ የክልሉ መንግሥት ዝግጅት እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

ለዚህም በቢሾፍቱ፣ ነቀምት፣ አዳማ እና ሻሸመኔ ከተሞች የሚገኙ የቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ ማዕከላት የተመረጡ የፈጠራ ውጤቶችን በስፋት አምርተው ለገበያ እንዲያቀርቡ እየተሰራ መሆኑን አውስተዋል።


በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች የሜዳሊያ፣ የዋንጫ፣ የታብሌትና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026