የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮ ክህሎት ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ገበያው የሚፈልገውን ቴክኖሎጂ ለማበልጸግ እያስቻለ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 24/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮ ክህሎት ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ ገበያው የሚፈልገውን ቴክኖሎጂ ለማበልጸግ እያስቻለ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ፡፡

ኢትዮ ክህሎት አራተኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ ከሚያዚያ 27 እስከ ግንቦት 2 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል መርኃ ግብሩን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም፤ ኢትዮ ክህሎት ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የስልጠና ጥራትን ለማረጋገጥ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ መሆኑን ተናግረዋል።

መርኃ ግብሩ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተወዳድረው አሸናፊ የሆኑ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክህሎትና የቴክኖሎጂ ውድድር መሆኑን አስታውቀዋል።

የክህሎት ልማት ሀገርን ተወዳዳሪ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ ውድድሩ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች ለማላቅ፤ ቀሪዎቹን በብቃት ለመፈጸም ያስችላል ብለዋል፡፡

የክህሎት ውድድሩ ከኢትዮጵያ ፍላጎት ጋር የሚጣጣሙ እና ከገበያው ፍላጎት ጋር የሚያስተሳስሩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች ላይ የሚያተኩር መሆኑንም ጠቁመዋል።

ኢትዮ ክህሎት ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ ገበያው የሚፈልገውን ቴክኖሎጂ ማበልጸግ ማስቻሉንም ገልጸዋል፡፡

በ2016 በጀት ዓመት 81 ቴክኖሎጂዎች መልማታቸውን እና በዘንድሮው በጀት ዓመት ደግሞ 180 ተሳታፊዎች 99 ቴክኖሎጂዎችን በማልማት ሂደት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የአርበኝነት ምዕራፍ ጀምራለች ያሉት ሚኒስትሯ፤ የክህሎት ውድድሩ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በአራት ማዕከላት በ22 ዘርፎች የሚካሄድ ውድድር የቱሪዝም አገልግሎት ዘርፉን የሚያነቃቃ መርኃ ግብር እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

በመርኃ ግብሩ ኢትዮጵያን በዘርፉ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርጉ 70 አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ለእይታ ይቀርቡበታል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026