የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በቴክኖሎጂና ምህንድስና ዘርፎች የምርምር ስራዎችን ለሀገር እድገት ለማዋል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል

May 6, 2025

IDOPRESS

ሐዋሳ፤ሚያዚያ 24/2017 (ኢዜአ)፦በቴክኖሎጂና ምህንድስና ዘርፎች የምርምር ስራዎችን ለሀገር እድገት ለማዋል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ፡፡


ለሁለት ቀናት የሚካሄደው 7ኛውን ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በዛሬው እለት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መካሄድ ጀምሯል።


የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዚዳንት ታፈሰ ማቲዎስ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥በምህንድስናና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የሚደረጉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር እንደሃገር የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡


በተለይም በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚታዩ ማነቆዎችን ለመፍታት ዩኒቨርሲቲው አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችንና ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማካሄድ ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው ብለዋል፡፡


በዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሚዘጋጀው የምርምር ኮንፈረንስም በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ተቀናጅቶ በመፍታት ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ውጤቶች የሚገኝበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በዚህም ዩኒቨርሲቲው ከሀዋሳና ከይርጋለም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ጋር በመቀናጀት የሚወገዱ ተፈረ ምርቶችን መልሶ ለመጠቀም የሚያስችሉ ችግር ፈቺ ምርምሮችን አድርጓል ብለዋል፡፡


በቴክኖሎጂና ምህንድስና ዘርፎች የምርምር ስራዎችን ለሀገር እድገት ለማዋል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።


በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ምህረት ደናንቶ (ዶ/ር) በምርምር ኮንፈረንሱ በፈጠራ ላይ ያተኮሩ 32 ጥናታዊ የምርምር ስራዎች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው መሆኑን ጠቁመዋል።


"ኢትዮጵያን በምህንድስናና ቴክኖሎጂ ፈጠራ መድረስ" በሚል መሪ ሃሳብ ከተዘጋጀው መድረግ የሚገኙ ውጤችም የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡


ከዚህ ቀደም በኢንስቲትዩቱ የተሰሩ የምርምር ስራዎችን ወደ ፈጠራ በመቀየር ከውጭ የሚገቡ ማሽነሪዎችን በሃገር ውስጥ የመተካት፣ሰው ሰራሽ አካል የማምረትና ከወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶች የተለያዩ ስራዎች የተሰሩ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡


በተለይም በውሃ ማእድንና ኢነርጂ ዘርፍ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ዩኒቨርሲቲው ጥናትን መሰረት ያደረገ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።


በመድረኩ የተገኙት የሲዳማ ክልል ውሃ ማእድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ከበደ ጋኖሌ፤ በክልሉ በማእድን ዘርፍ ያሉ አቅሞችን የመለየት፣በመስኖና በመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ላይ በተሰሩ በጥናት የተደገፉ ስራዎች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡


በመድረኩ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ምሁራን የምርምር ስራዎቻቸውን አቅርበው ውይይት እንደተደረገባቸውም ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026