የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በቴክኖሎጂና ምህንድስና ዘርፎች የምርምር ስራዎችን ለሀገር እድገት ለማዋል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል

May 6, 2025

IDOPRESS

ሐዋሳ፤ሚያዚያ 24/2017 (ኢዜአ)፦በቴክኖሎጂና ምህንድስና ዘርፎች የምርምር ስራዎችን ለሀገር እድገት ለማዋል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ፡፡


ለሁለት ቀናት የሚካሄደው 7ኛውን ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በዛሬው እለት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መካሄድ ጀምሯል።


የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዚዳንት ታፈሰ ማቲዎስ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥በምህንድስናና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የሚደረጉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር እንደሃገር የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡


በተለይም በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚታዩ ማነቆዎችን ለመፍታት ዩኒቨርሲቲው አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችንና ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማካሄድ ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው ብለዋል፡፡


በዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሚዘጋጀው የምርምር ኮንፈረንስም በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ተቀናጅቶ በመፍታት ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ውጤቶች የሚገኝበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በዚህም ዩኒቨርሲቲው ከሀዋሳና ከይርጋለም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ጋር በመቀናጀት የሚወገዱ ተፈረ ምርቶችን መልሶ ለመጠቀም የሚያስችሉ ችግር ፈቺ ምርምሮችን አድርጓል ብለዋል፡፡


በቴክኖሎጂና ምህንድስና ዘርፎች የምርምር ስራዎችን ለሀገር እድገት ለማዋል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።


በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ምህረት ደናንቶ (ዶ/ር) በምርምር ኮንፈረንሱ በፈጠራ ላይ ያተኮሩ 32 ጥናታዊ የምርምር ስራዎች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው መሆኑን ጠቁመዋል።


"ኢትዮጵያን በምህንድስናና ቴክኖሎጂ ፈጠራ መድረስ" በሚል መሪ ሃሳብ ከተዘጋጀው መድረግ የሚገኙ ውጤችም የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡


ከዚህ ቀደም በኢንስቲትዩቱ የተሰሩ የምርምር ስራዎችን ወደ ፈጠራ በመቀየር ከውጭ የሚገቡ ማሽነሪዎችን በሃገር ውስጥ የመተካት፣ሰው ሰራሽ አካል የማምረትና ከወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶች የተለያዩ ስራዎች የተሰሩ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡


በተለይም በውሃ ማእድንና ኢነርጂ ዘርፍ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ዩኒቨርሲቲው ጥናትን መሰረት ያደረገ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።


በመድረኩ የተገኙት የሲዳማ ክልል ውሃ ማእድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ከበደ ጋኖሌ፤ በክልሉ በማእድን ዘርፍ ያሉ አቅሞችን የመለየት፣በመስኖና በመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ላይ በተሰሩ በጥናት የተደገፉ ስራዎች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡


በመድረኩ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ምሁራን የምርምር ስራዎቻቸውን አቅርበው ውይይት እንደተደረገባቸውም ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026