የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የቡሬ የተቀናጀ አግሮ-ኢንዱስትሪን በተሟላ አቅም ወደ ልማት ለማስገባት በቁርጠኝነት እየተሰራ ነው

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦የቡሬ የተቀናጀ አግሮ-ኢንዱስትሪን በተሟላ አቅም ወደልማት ለማስገባት በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተሞች ልማት ክላስተር አስተባባሪና ከተሞችና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

የአማራ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በቡሬ የተቀናጀ አግሮ-ኢንዱስትሪ ውስጥ ከገቡ አልሚ ባለሀብቶች ጋር የውይይት መድረክ በማካሄድ ላይ ይገኛል።

በመድረኩ የተገኙት ዶክተር አሕመዲን መሐመድ ግብዓትና የኃይል አቅርቦት ለኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅም መሰረታዊ ጉዳይ ነው ብለዋል።

በዚህም በ260 ሔክታር መሬት ላይ በለማው የቡሬ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሰባት የገጠር ሽግግር ማዕከላትን ጨምሮ ምቹ የመሠረተ ልማት መዘርጋቱን ገልጸዋል።

በቀጣይም የቡሬ የተቀናጀ አግሮ-ኢንዱስትሪን በተሟላ አቅም ወደ ልማት በማስገባት ለአልሚ ባለሃብቶች ተገቢውን ድጋፍ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

መድረኩ የቡሬ አግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበትን ሁኔታ ለመረዳት፣ ለመማማርና ልምድ ለመቀያየር እንዲሁም በስራ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን መፍትሔ ለመስጠት የሚረዳ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የመሠረተ ልማትና አቅም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈፃሚ አድማሱ ይፍሩ፥ መንግስት የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ ለኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅም የሆኑ ፓርኮች መገንባታቸውን ተናግረዋል።

በዚህም በቡሬ የተቀናጀ አግሮ-ኢንዱስትሪ የሚስተዋሉትን የኃይል አቅርቦትና ተያያዥ ችግሮች መፍትሔ በመስጠት ወደተሟላ የምርታማነት አቅም ለማስገባት ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

ባለሀብቶችም ከሀይል አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚያነሱት ጥያቄ በቀጣይ የሚቀረፍ መሆኑን በመገንዘብ በሙሉ አቅም ወደስራ ለመግባት ዝግጁ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብርሃኑ ጣምያለው፥ በክልሉ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ አቅም የሚሆን ሰፊ የተፈጥሮ ሃብት መኖሩን ገልጸዋል።

በዚህም ክልሉን የኢንዱስትሪ ማዕከል ማድረግ የሚያስችሉ የኢንቨስትመንትና የኢንዱስትሪ መሰረተ ልማት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በቀጣይም የቡሬ የተቀናጀ አግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርክን ጨምሮ በሌሎች የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የተሰማሩ አልሚዎችን ወደተማላ የማምረት አቅም ለማሸጋገር ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ አንስተዋል።

በቡሬ የተቀናጀ አግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርክ አልሚ ምግብና የምግብ ዘይት ጨምሮ የግብርና ምርት ውጤቶችን በማቀነባበር ለገበያ እያቀረበ እንደሚገኝም ተገልጿል።

በምክክር መድረኩ ላይ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ አመራሮች፣በቡሬ የተቀናጀ አግሮ ኢንዳስትሪ በኢንቨስትመንት የገቡ ባለሃብቶችና የልማት አጋሮች ተገኝተዋል።

በፓርኩ የገጠር ሽግግር ማዕከላት ወደስራ የገቡ አልሚዎችና በግንባታ ላይ ያሉትን አሁናዊ ሁኔታ የሚያሳይ መነሻ ጽሁፍ ቀርቦ ምክክር እየተካሄደበት ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026