ባህር ዳር፤ሚያዚያ 27/2017(ኢዜአ)፦በባህርዳር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን 17 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የከተማ ከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።
አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፥ ባህር ዳር ከተማ ተመራጭ የቱሪስትና የኢንቨስትመንት ማዕከል እንድትሆን ለመሰረተ ልማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል።
በዚህም በከተማዋ በተለያየ ጊዜ ተጀምረው በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ 22 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የአስፋልት መንገዶች እንዳሉ ተናግረዋል።
መንገዶቹም ከ20 እስከ 40 ሜትር ስፋት ያላቸውና የእግረኛ፣የሳይክል፣ የአረንጓዴ ልማትና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ያሟሉ ናቸው ብለዋል።
በግንባታ ሂደት ውስጥ ካሉትም 17 ኪሎ ሜትር የሚሆነውን የአስፋልት መንገድ በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በተጨማሪም የኮሪደር ልማት፣ የስማርት ሲቲ እና የዲጂታላይዜሽን ተግባራትን በማከናወን ከተማዋን ለማዘመን የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ብለዋል።
የአማራ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ በባህር ዳር ከተማ እየተሰሩ ያሉ መሰረተ ልማቶች ከተማዋን ውብ፣ሳቢና ማራኪ ለማድረግ የሚያስችሉ ናቸው።
ይህም ከተማዋን ለቱሪዝም፣ለኢንቨስትመንት፣ ለኑሮና ለንግድ ተመራጭ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፥ ለስኬቱ ተገቢው ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል።
የክልሉን ሰላም ከማጽናት ጎን ለጎን ከተሞችን የሚያነቃቁ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፣የከተማ አመራሮች ተቀራራቢ ተልዕኮና እይታ ይዘው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
የክልሉና የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በከተማዋ የሚገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ተመልክተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026