ባህር ዳር፤ሚያዚያ 27/2017(ኢዜአ)፦በባህርዳር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን 17 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የከተማ ከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።
አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፥ ባህር ዳር ከተማ ተመራጭ የቱሪስትና የኢንቨስትመንት ማዕከል እንድትሆን ለመሰረተ ልማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል።
በዚህም በከተማዋ በተለያየ ጊዜ ተጀምረው በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ 22 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የአስፋልት መንገዶች እንዳሉ ተናግረዋል።
መንገዶቹም ከ20 እስከ 40 ሜትር ስፋት ያላቸውና የእግረኛ፣የሳይክል፣ የአረንጓዴ ልማትና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ያሟሉ ናቸው ብለዋል።
በግንባታ ሂደት ውስጥ ካሉትም 17 ኪሎ ሜትር የሚሆነውን የአስፋልት መንገድ በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በተጨማሪም የኮሪደር ልማት፣ የስማርት ሲቲ እና የዲጂታላይዜሽን ተግባራትን በማከናወን ከተማዋን ለማዘመን የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ብለዋል።
የአማራ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ በባህር ዳር ከተማ እየተሰሩ ያሉ መሰረተ ልማቶች ከተማዋን ውብ፣ሳቢና ማራኪ ለማድረግ የሚያስችሉ ናቸው።
ይህም ከተማዋን ለቱሪዝም፣ለኢንቨስትመንት፣ ለኑሮና ለንግድ ተመራጭ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፥ ለስኬቱ ተገቢው ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል።
የክልሉን ሰላም ከማጽናት ጎን ለጎን ከተሞችን የሚያነቃቁ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፣የከተማ አመራሮች ተቀራራቢ ተልዕኮና እይታ ይዘው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
የክልሉና የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በከተማዋ የሚገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ተመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025