የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በባህር ዳር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን 17 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታን ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

May 6, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ሚያዚያ 27/2017(ኢዜአ)፦በባህርዳር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን 17 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የከተማ ከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።


አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፥ ባህር ዳር ከተማ ተመራጭ የቱሪስትና የኢንቨስትመንት ማዕከል እንድትሆን ለመሰረተ ልማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል።


በዚህም በከተማዋ በተለያየ ጊዜ ተጀምረው በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ 22 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የአስፋልት መንገዶች እንዳሉ ተናግረዋል።


መንገዶቹም ከ20 እስከ 40 ሜትር ስፋት ያላቸውና የእግረኛ፣የሳይክል፣ የአረንጓዴ ልማትና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ያሟሉ ናቸው ብለዋል።


በግንባታ ሂደት ውስጥ ካሉትም 17 ኪሎ ሜትር የሚሆነውን የአስፋልት መንገድ በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።


በተጨማሪም የኮሪደር ልማት፣ የስማርት ሲቲ እና የዲጂታላይዜሽን ተግባራትን በማከናወን ከተማዋን ለማዘመን የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ብለዋል።


የአማራ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ በባህር ዳር ከተማ እየተሰሩ ያሉ መሰረተ ልማቶች ከተማዋን ውብ፣ሳቢና ማራኪ ለማድረግ የሚያስችሉ ናቸው።


ይህም ከተማዋን ለቱሪዝም፣ለኢንቨስትመንት፣ ለኑሮና ለንግድ ተመራጭ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፥ ለስኬቱ ተገቢው ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል።


የክልሉን ሰላም ከማጽናት ጎን ለጎን ከተሞችን የሚያነቃቁ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፣የከተማ አመራሮች ተቀራራቢ ተልዕኮና እይታ ይዘው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።


የክልሉና የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በከተማዋ የሚገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026