የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የካዴፕ የ10 ዓመት ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነ

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 27/2017 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዴፕ) የ10 ዓመት ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ማድረጊያ ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ይፋ ሆኗል።


በስነ ስርዓቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ፣የደቡብ አፍሪካ የግብርና ሚኒስትር ጆን ስቴንሁይሰን፣ የህብረቱ አመራሮች፣ የቀጣናዊ ተቋማት ኃላፊዎች፣የህብረቱ አባል ሀገራት ተወካዮች፣የልማት አጋሮች እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።


በመክፈቻ ስነ ስርዓቱ ላይ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ስትራቴጂው እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ማድረጋቸውን የአፍሪካ ህብረት ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።


ስትራቴጂው እና የማስፈጸሚያ የድርጊት መርሃ ግብሩ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚቆይ ነው።


ዘላቂ ምርታማነትን፣አግሮ ኢንዱስትሪ እና ንግድን የበለጠ ማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት መጠንን በማሳደግ የስነ ምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን ማሳለጥ እንዲሁም የምግብ እና የስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ከስትራቴጂው ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።


ለዜጎች ሁሉን አካታች እና እኩል የሆነ የኑሮ ሁኔታን መፍጠር፣ የማይበገር ስርዓተ-ምግብ መገንባት እና የምግብ ስርዓት አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የካዴፕ ግቦች ናቸው።


በስትራቴጂው የአፍሪካን የግብርና ምርታማነት እ.አ.አ በ2035 በ45 በመቶ ለማሳደግ እቅድ ተይዟል።


የአፍሪካ ህብረት ካዴፕን አስመልክቶ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በዩጋንዳ ካምፓላ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ አዲሱን የ10 ዓመት ስትራቴጂ ማፅደቁ የሚታወስ ነው።


የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም(ካዴፕ) የአጀንዳ 2063 አህጉራዊ ማዕቀፍ ሲሆን የአፍሪካ ሀገራት በግብርና መር ልማት ኢኮኖሚያቸውን በማሳደግ ረሃብን እንዲያስወግዱ እና ድህነትን እንዲቀንሱ ማድረግን ዋነኛ አላማው አድርጓል።


በካዴፕ አማካኝነት የአፍሪካ መንግስታት ከዓመታዊ ጥቅል ምርታቸው (ዲጂፒ) ቢያንስ 10 በመቶ የሚሆነውን ለግብርና እና ገጠር ልማት ለመመደብ ተስማምተዋል።


በዚህም ሀገራቱ የግብርና ዘርፉን በየዓመቱ ቢያንስ በስድስት በመቶ ለማሳደግ አቅደው በመስራት ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026