የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የካዴፕ የ10 ዓመት ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነ

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 27/2017 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዴፕ) የ10 ዓመት ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ማድረጊያ ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ይፋ ሆኗል።


በስነ ስርዓቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ፣የደቡብ አፍሪካ የግብርና ሚኒስትር ጆን ስቴንሁይሰን፣ የህብረቱ አመራሮች፣ የቀጣናዊ ተቋማት ኃላፊዎች፣የህብረቱ አባል ሀገራት ተወካዮች፣የልማት አጋሮች እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።


በመክፈቻ ስነ ስርዓቱ ላይ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ስትራቴጂው እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ማድረጋቸውን የአፍሪካ ህብረት ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።


ስትራቴጂው እና የማስፈጸሚያ የድርጊት መርሃ ግብሩ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚቆይ ነው።


ዘላቂ ምርታማነትን፣አግሮ ኢንዱስትሪ እና ንግድን የበለጠ ማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት መጠንን በማሳደግ የስነ ምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን ማሳለጥ እንዲሁም የምግብ እና የስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ከስትራቴጂው ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።


ለዜጎች ሁሉን አካታች እና እኩል የሆነ የኑሮ ሁኔታን መፍጠር፣ የማይበገር ስርዓተ-ምግብ መገንባት እና የምግብ ስርዓት አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የካዴፕ ግቦች ናቸው።


በስትራቴጂው የአፍሪካን የግብርና ምርታማነት እ.አ.አ በ2035 በ45 በመቶ ለማሳደግ እቅድ ተይዟል።


የአፍሪካ ህብረት ካዴፕን አስመልክቶ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በዩጋንዳ ካምፓላ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ አዲሱን የ10 ዓመት ስትራቴጂ ማፅደቁ የሚታወስ ነው።


የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም(ካዴፕ) የአጀንዳ 2063 አህጉራዊ ማዕቀፍ ሲሆን የአፍሪካ ሀገራት በግብርና መር ልማት ኢኮኖሚያቸውን በማሳደግ ረሃብን እንዲያስወግዱ እና ድህነትን እንዲቀንሱ ማድረግን ዋነኛ አላማው አድርጓል።


በካዴፕ አማካኝነት የአፍሪካ መንግስታት ከዓመታዊ ጥቅል ምርታቸው (ዲጂፒ) ቢያንስ 10 በመቶ የሚሆነውን ለግብርና እና ገጠር ልማት ለመመደብ ተስማምተዋል።


በዚህም ሀገራቱ የግብርና ዘርፉን በየዓመቱ ቢያንስ በስድስት በመቶ ለማሳደግ አቅደው በመስራት ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025