አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 27/2017 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዴፕ) የ10 ዓመት ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ማድረጊያ ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ይፋ ሆኗል።
በስነ ስርዓቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ፣የደቡብ አፍሪካ የግብርና ሚኒስትር ጆን ስቴንሁይሰን፣ የህብረቱ አመራሮች፣ የቀጣናዊ ተቋማት ኃላፊዎች፣የህብረቱ አባል ሀገራት ተወካዮች፣የልማት አጋሮች እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
በመክፈቻ ስነ ስርዓቱ ላይ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ስትራቴጂው እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ማድረጋቸውን የአፍሪካ ህብረት ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ስትራቴጂው እና የማስፈጸሚያ የድርጊት መርሃ ግብሩ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚቆይ ነው።
ዘላቂ ምርታማነትን፣አግሮ ኢንዱስትሪ እና ንግድን የበለጠ ማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት መጠንን በማሳደግ የስነ ምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን ማሳለጥ እንዲሁም የምግብ እና የስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ከስትራቴጂው ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።
ለዜጎች ሁሉን አካታች እና እኩል የሆነ የኑሮ ሁኔታን መፍጠር፣ የማይበገር ስርዓተ-ምግብ መገንባት እና የምግብ ስርዓት አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የካዴፕ ግቦች ናቸው።
በስትራቴጂው የአፍሪካን የግብርና ምርታማነት እ.አ.አ በ2035 በ45 በመቶ ለማሳደግ እቅድ ተይዟል።
የአፍሪካ ህብረት ካዴፕን አስመልክቶ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በዩጋንዳ ካምፓላ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ አዲሱን የ10 ዓመት ስትራቴጂ ማፅደቁ የሚታወስ ነው።
የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም(ካዴፕ) የአጀንዳ 2063 አህጉራዊ ማዕቀፍ ሲሆን የአፍሪካ ሀገራት በግብርና መር ልማት ኢኮኖሚያቸውን በማሳደግ ረሃብን እንዲያስወግዱ እና ድህነትን እንዲቀንሱ ማድረግን ዋነኛ አላማው አድርጓል።
በካዴፕ አማካኝነት የአፍሪካ መንግስታት ከዓመታዊ ጥቅል ምርታቸው (ዲጂፒ) ቢያንስ 10 በመቶ የሚሆነውን ለግብርና እና ገጠር ልማት ለመመደብ ተስማምተዋል።
በዚህም ሀገራቱ የግብርና ዘርፉን በየዓመቱ ቢያንስ በስድስት በመቶ ለማሳደግ አቅደው በመስራት ላይ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025