የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የክልሉ አርሶ አደሮች በቡና እና ቅመማ ቅመም ልማት የተሻለ ጥቅም እያገኙ ነው

May 7, 2025

IDOPRESS

ዱራሜ፤ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተለያዩ ዞኖች የሚገኙ አርሶ አደሮች በቡና እና ቅመማ ቅመም ልማት የተሻለ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።


ከማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ወደ 7 ሺህ ቶን የሚጠጋ የቡና እና የቅመማ ቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡም ተገልጿል።


በከምባታ ዞን ሀደሮ ጡንጦ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ወንድሙ ሱጋሞ እንደገለፁት፥ በሁለት ሄክታር ማሳቸው ላይ ዝንጅብል ማልማት ከጀመሩ ሁለት ዓመታት አስቆጥረዋል፡፡


ዝንጅብልን በሄክታር እስከ አንድ መቶ ኩንታል እያመረቱ መሆኑን የገለፁት አርሶ አደሩ፥ ምርቱን ለገበያ በማቅረብም ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡


ሌላኛውና በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ አና በሌሳ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ግዛቸው በየነ፥ ከሌላ የግብርና ስራቸው ጎን ለጎን ቡና በማልማት ተጠቃሚ መሆን ከጀመሩ መሰንበታቸውን ተናግረዋል፡፡


በዚህ ዓመት በውስን መሬት እስከ አስር ኩንታል የቡና ምርት ማግኘታቸውንና ተጠቃሚነታቸውን ማሻሻል መቻላቸውን ጠቁመዋል፡፡


በተለይም የቡናው ዘርፍ ላይ መስራት የተሻለ ገቢ ለማግኘት እንደሚረዳ ያነሱት አርሶ አደሩ፥ ባላቸው የእርሻ ቦታ ላይ ቡናን በማልማት ተጠቃሚ ለመሆን እየሰሩ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡


የክልሉ ቡና እና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ቶፊቅ ጀዋር፤ በ2016/17 የምርት ዘመን በቡና እና የቅመማ ቅመም ምርቶች 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዶ መሰራቱን ተናግረዋል።


በምርት ዘመኑ እስካሁን 3 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል መገኘቱን ገልጸው ከዚህም 2 ሚሊዮን ኩንታሉ የዝንጅብል ምርት መሆኑን ጠቅሰዋል።


በክልሉ በዋናነት በርበሬ፣ሮዝመሪ፣ዝንጅብል፣ ኮሰረትን ጨምሮ ሌሎችም ጨምሮ የቡና እና ቅመማ ቅመም ምርቶችን ለማምረት የሚያስችል እምቅ አቅም ያለው መሆኑን ገልጸዋል።


በቡና ምርት ብቻ በተያዘው በጀት ዓመት 2 ሺህ 400 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ በዘጠኝ ወራት ብቻ 1 ሺህ 967 ቶን ቡና ማቅረብ ተችሏል ብለዋል።


በክልሉ በዚህ ዓመት ከበልግ ወቅት ጀምሮ እስከ ነሐሴ አጋማሽ የሚተከል ከ44 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኝ ለተከላ መዘጋጀቱንም ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025