አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 28/2017(ኢዜአ)፡-በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍ በተለይም የተግባር ልምምድ ላይ የግሉ ሴክተር ሚናውን በበቂ መጠን ሊወጣ እንደሚገባ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ገለጸ።
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ስርዓተ ግንባታ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በሚል አውደጥናት ተካሂዷል።
በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ ዶክተር አማረ ማተቡ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍ ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችና መፍትሄዎች ላይ ያተኮረ ጥናት አቅርበዋል።
በጥናቱ የዘርፉ ዋና ዋና ችግሮች የተለዩ መሆኑን ገልጸዋል።
የግሉ ዘርፍ በተለይ ኢንዱስትሪው ሚናውን በበቂ ሁኔታ መወጣት ባለመቻሉ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍ ላይ የተግባር ልምምድ ክፍተቶች መኖራቸውን ጥናቱ ያመለክታል ብለዋል።
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ስርዓተ ትምህርቱ የገበያውን ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ እንዲከለስና ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት ከማመላከት አንጻር ከግሉ ዘርፍ ብዙ ሰራዎች እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።
የተግባር ልምምድ ስልጠና የሚሰጥባቸው ኢንዱስትሪዎች ለስልጠናው ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ስታንዳርዱን የጠበቀ ስልጠና ከመስጠትና ብቃት ያላቸውን አሰልጣኞች ከመመደብ አንጻር ሰፊ ክፍተቶች አሉ ብለዋል።
በመሆኑም በተግባር ልምምድ ስልጠናው ላይ የሚፈለገው ስኬት እንዳይገኝ ማድረጉን ተናግረዋል።
ዘርፉ ለተግባር ልምምድ ግብአቶችን፣ መሳሪያዎችን ለማሟላት ከፍተኛ በጀት የሚጠይቅ በመሆኑ የፋይናንስ እጥረት አንዱ ተግዳሮት መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ለዚህም የግሉ ሴክተር ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባው አስረድተዋል።
በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አማካሪ አቶ አዝመራ ከበደ ኢኮኖሚያዊ ሽግግር የሚረጋገጠው ብቃት ያለው የሰው ሀይል ለኢንዱስትሪው ማቅረብ ሲቻል በመሆኑ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፉን ማሳደግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
የግሉ ዘርፍ ተደራጅቶ የቴክኖሎጂና የሰው ሀይል ልማት ላይ በፖለሲ ተደግፎ እንዲሰራ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ ትምህርትና ስልጠና ፖለሲ ክለሳ፣ ስትራቴጂ ዝግጅት፣ ተከታታይ የስራ ላይ ስልጠናዎች እንዲሁም የሪፎርም ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025