
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት በማምረት ውጤታማ አንድንሆን አስችሎናል ሲሉ በዘርፉ የተሰማሩ አምራቾች ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሚያዚያ 25 እስከ 29 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆየውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ288 በላይ አምራቾች እየተሳተፉበት ይገኛሉ፡፡
ኢዜአ በቦታው በመገኘት ያነጋገራቸው በጨርቃጨርቅ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ አምራቾች እንዳሉት ኤክስፖው ምርቶቻቸውን ለማስተዋወቅና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡
የሮንሸንግ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ተወካይ እዝራ ዮሴፍ እንዳስታወቁት አሁን ላይ በንቅናቄው በመታገዝ ከውጭ ይገቡ የነበሩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት ጀምረዋል፡፡
ኤክስፖው አምራቾች እርስ በእርሳችን እንድንተዋወቅና የገበያ ትስስር እንድንፈጥር አስችሎናልም ነው ያሉት፡፡
የማርስ ዲዛይን መስራች እና ባለቤት ወይዘሮ ማርሳለም ሁሴን በበኩሏ፤ ኤክስፖው አምራቾችን የሚያገናኝ እና የገበያ ትስስር የሚፈጥር መሆኑን ተናግራለች፡፡
የሳዊን ጋርመንት መስራች እና ባለቤት አቶ ሽመልስ አስናቀ በኤክስፖው ከጥሬ ዕቃ አቅራቢዎችና የእኛን ምርት ከሚፈልጉ ነጋዴዎች ጋር ለመገናኘት ችለናል ብለዋል፡፡
የኤርኮ ታክስታይል ተወካይ አቶ ኤፍሬም በቀለ ከጨርቃጨርቅ ተረፈ ምርቶች የስፌት ክርና መሰል ግብዓቶችን እያመረቱ እንደሚገኙ ተናግሯል፡፡
አምራቾቹ አክለውም በተለይ እንደ ሀገር የውጭ ምንዛሪን በማዳን በኩል ተኪ ምርት በማምረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የሮንሸንግ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ተወካይ እዝራ ዮሴፍ እንደ ሀገር የውጭ ምንዛሪ የሚያድኑ ተኪ ምርቶችን ለገበያ እያቀረብን እንገኛለን ብለዋል፡፡
የማርስ ዲዛይን መስራች እና ባለቤት ወይዘሮ ማርሳለም ሁሴን ኤክስፖው ምርታችንን በማስተዋወቅ ለውጭ ገበያ የምናቀርብበትን ዕድል ፈጥሮልናል ብላለች፡፡
የሳዊን ጋርመንት መስራች እና ባለቤት አቶ ሽመልስ አስናቀም ንቅናቄው ከውጭ ተመርተው ይመጡ የነበሩ ሸሚዞችንና የልጆች ንፅህና መጠበቂያ በሀገር ውስጥ በማምረት የውጭ ምንዛሪ ማዳን ችለናል ነው ያሉት፡፡
በሀገር ውስጥ የምናመርተው ግብዓት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ምርቶችን በመተካት በኩል የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ሲሉ የተናገሩት ደግሞ የኤርኮ ቴክስታይል ተወካይ አቶ ኤፍሬም በቀለ ተናግረዋል፡፡
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026