
ቡታጅራ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ።
በክልሉ በምስራቅ ጉራጌ ዞን የተለያዩ መዋቅሮች ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

የመስኖ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድ፣ የዘመናዊ ተንጠልጣይ ድልድይና የመደበኛ ድልድዮች ግንባታ ሥራዎች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ከተደረጉት መካከል ይገኙበታል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት መንግሥት ከዜጎች የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።
በዚህም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚረዱ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ ወስጥ ገንብቶ ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን ገልጸዋል።

ከእነዚህ ውስጥ ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ ፕሮጀክቶችን ለአብነት አንስተዋል።
በክልሉ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር ኢ/ር) በበኩላቸው መንግስት የዜጎችን የልማት ጥያቄዎች በፍትሃዊነት ለመመለስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት።
ሚኒስቴሩ በክልሉ በመንግስትና በአጋር አካላት ትብብር ከ7 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ 44 የመስኖና የንፁህ መጠጥ ውሃን ተደራሽ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ(ዶ/ር) በበኩላቸው ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት ፕሮጀክቶች መንግሥት ለዜጎች ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ያለውን ተነሳሽነት የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
በምስራቅ ጉራጌ ዞን ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ተገንብተው ዛሬ ለአገልግሎት የበቁት ፕሮጀክቶች ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ምርታማነትን ለማሳደግና የአርሶ አደሩን ምርትን ወደ ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡
በፕሮጀክቶች የምረቃ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ከተመረቁት የልማት ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በ500 ሚሊዮን ብር ለሚገነባው የቡታጅራ ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ጣቢያ ፕሮጀክት የመሰረተ ድንጋይ በርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) እና በውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር ኢ/ር) እንደተቀመጠ መዘገቡ ይተወሳል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025