የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)

May 7, 2025

IDOPRESS

ቡታጅራ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ።

በክልሉ በምስራቅ ጉራጌ ዞን የተለያዩ መዋቅሮች ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።


የመስኖ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድ፣ የዘመናዊ ተንጠልጣይ ድልድይና የመደበኛ ድልድዮች ግንባታ ሥራዎች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ከተደረጉት መካከል ይገኙበታል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት መንግሥት ከዜጎች የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።

በዚህም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚረዱ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ ወስጥ ገንብቶ ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን ገልጸዋል።


ከእነዚህ ውስጥ ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ ፕሮጀክቶችን ለአብነት አንስተዋል።

በክልሉ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር ኢ/ር) በበኩላቸው መንግስት የዜጎችን የልማት ጥያቄዎች በፍትሃዊነት ለመመለስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት።

ሚኒስቴሩ በክልሉ በመንግስትና በአጋር አካላት ትብብር ከ7 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ 44 የመስኖና የንፁህ መጠጥ ውሃን ተደራሽ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ(ዶ/ር) በበኩላቸው ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት ፕሮጀክቶች መንግሥት ለዜጎች ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ያለውን ተነሳሽነት የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ተገንብተው ዛሬ ለአገልግሎት የበቁት ፕሮጀክቶች ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ምርታማነትን ለማሳደግና የአርሶ አደሩን ምርትን ወደ ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

በፕሮጀክቶች የምረቃ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

ከተመረቁት የልማት ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በ500 ሚሊዮን ብር ለሚገነባው የቡታጅራ ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ጣቢያ ፕሮጀክት የመሰረተ ድንጋይ በርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) እና በውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር ኢ/ር) እንደተቀመጠ መዘገቡ ይተወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026