
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪው በተኪ ምርትና በስራ ዕድል ፈጠራ ገንቢ ሚና እንዲወጣ ማገዙን አምራቾች ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።
ኢዜአ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምርትና አገልግሎታቸውን ይዘው የቀረቡ አምራቾችን ተዘዋውሮ አነጋግሯል።
የኢናስ ሶሊሽን ተወካይ ዮናስ ሸዋንግዛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የአምራች ኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግና በሥራ ዕድል ፈጠራ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል።
ፋብሪካቸው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚጠይቀውን ብረት በአገር ውስጥ በማምረት ተስፋ ሰጪ አቅም እየፈጠረ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የሸንጋይ ማሽነሪ ሥራ አስፈፃሚ ብርቱካን ጌታሁን በበኩላቸው ለኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከፍተኛ አቅም የሚሆኑ የግንባታ ማሽነሪ እያመረቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው የተሰጠው ትኩረት በተኪ ምርትና በስራ ዕድል ፈጠራ ገንቢ ሚና እንዲወጡ እያስቻላቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ኤክስፖው በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቁ የብረታ ብረት ውጤቶችን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር ለመፍጠር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የፔጋስ ኢንጂነሪንግ ተወካይ ሰለሞን ታደሰ ተናግረዋል።
ድርጅታቸው ከውጭ የሚገቡ የተሽከርካሪ አካላትን በሀገር ውስጥ በማምረት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀው በቀጣይም በተኪ ምርት ላይ በስፋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
የዲኬ ኦልድ ኩባንያ ተወካይ ወይዘሮ የምስራች ንጋቱ ኤክስፖው ምርትና አገልግሎታቸውን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር የሚያገኙበትን መልካም አጋጣሚ መፍጠሩን አስረድተዋል።
ንቅናቄው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለማምረት ከማስቻሉ በላይ ሰፊ የስራ ዕድል ለመፍጠር የራሱን ሚና መጫወቱን አስረድተዋል፡፡
መንግስት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ዘርፉን ለማበረታታት እያደረገ የሚገኘው ድጋፍና ክትትል የምርታማነት አቅማቸውን ለማሳደግ ከፍተኛ ዕገዛ እያደረገላቸው እንደሚገኝ አስተያየት ሰጪዎቹ አረጋግጠዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026