
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪው በተኪ ምርትና በስራ ዕድል ፈጠራ ገንቢ ሚና እንዲወጣ ማገዙን አምራቾች ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።
ኢዜአ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምርትና አገልግሎታቸውን ይዘው የቀረቡ አምራቾችን ተዘዋውሮ አነጋግሯል።
የኢናስ ሶሊሽን ተወካይ ዮናስ ሸዋንግዛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የአምራች ኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግና በሥራ ዕድል ፈጠራ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል።
ፋብሪካቸው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚጠይቀውን ብረት በአገር ውስጥ በማምረት ተስፋ ሰጪ አቅም እየፈጠረ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የሸንጋይ ማሽነሪ ሥራ አስፈፃሚ ብርቱካን ጌታሁን በበኩላቸው ለኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከፍተኛ አቅም የሚሆኑ የግንባታ ማሽነሪ እያመረቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው የተሰጠው ትኩረት በተኪ ምርትና በስራ ዕድል ፈጠራ ገንቢ ሚና እንዲወጡ እያስቻላቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ኤክስፖው በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቁ የብረታ ብረት ውጤቶችን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር ለመፍጠር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የፔጋስ ኢንጂነሪንግ ተወካይ ሰለሞን ታደሰ ተናግረዋል።
ድርጅታቸው ከውጭ የሚገቡ የተሽከርካሪ አካላትን በሀገር ውስጥ በማምረት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀው በቀጣይም በተኪ ምርት ላይ በስፋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
የዲኬ ኦልድ ኩባንያ ተወካይ ወይዘሮ የምስራች ንጋቱ ኤክስፖው ምርትና አገልግሎታቸውን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር የሚያገኙበትን መልካም አጋጣሚ መፍጠሩን አስረድተዋል።
ንቅናቄው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለማምረት ከማስቻሉ በላይ ሰፊ የስራ ዕድል ለመፍጠር የራሱን ሚና መጫወቱን አስረድተዋል፡፡
መንግስት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ዘርፉን ለማበረታታት እያደረገ የሚገኘው ድጋፍና ክትትል የምርታማነት አቅማቸውን ለማሳደግ ከፍተኛ ዕገዛ እያደረገላቸው እንደሚገኝ አስተያየት ሰጪዎቹ አረጋግጠዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025