የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪው ገንቢ ሚና እንዲወጣ አግዟል

May 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪው በተኪ ምርትና በስራ ዕድል ፈጠራ ገንቢ ሚና እንዲወጣ ማገዙን አምራቾች ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።

ኢዜአ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምርትና አገልግሎታቸውን ይዘው የቀረቡ አምራቾችን ተዘዋውሮ አነጋግሯል።

የኢናስ ሶሊሽን ተወካይ ዮናስ ሸዋንግዛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የአምራች ኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግና በሥራ ዕድል ፈጠራ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል።

ፋብሪካቸው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚጠይቀውን ብረት በአገር ውስጥ በማምረት ተስፋ ሰጪ አቅም እየፈጠረ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የሸንጋይ ማሽነሪ ሥራ አስፈፃሚ ብርቱካን ጌታሁን በበኩላቸው ለኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከፍተኛ አቅም የሚሆኑ የግንባታ ማሽነሪ እያመረቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው የተሰጠው ትኩረት በተኪ ምርትና በስራ ዕድል ፈጠራ ገንቢ ሚና እንዲወጡ እያስቻላቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ኤክስፖው በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቁ የብረታ ብረት ውጤቶችን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር ለመፍጠር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የፔጋስ ኢንጂነሪንግ ተወካይ ሰለሞን ታደሰ ተናግረዋል።

ድርጅታቸው ከውጭ የሚገቡ የተሽከርካሪ አካላትን በሀገር ውስጥ በማምረት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀው በቀጣይም በተኪ ምርት ላይ በስፋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

የዲኬ ኦልድ ኩባንያ ተወካይ ወይዘሮ የምስራች ንጋቱ ኤክስፖው ምርትና አገልግሎታቸውን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር የሚያገኙበትን መልካም አጋጣሚ መፍጠሩን አስረድተዋል።

ንቅናቄው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለማምረት ከማስቻሉ በላይ ሰፊ የስራ ዕድል ለመፍጠር የራሱን ሚና መጫወቱን አስረድተዋል፡፡

መንግስት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ዘርፉን ለማበረታታት እያደረገ የሚገኘው ድጋፍና ክትትል የምርታማነት አቅማቸውን ለማሳደግ ከፍተኛ ዕገዛ እያደረገላቸው እንደሚገኝ አስተያየት ሰጪዎቹ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025