የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪው ገንቢ ሚና እንዲወጣ አግዟል

May 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪው በተኪ ምርትና በስራ ዕድል ፈጠራ ገንቢ ሚና እንዲወጣ ማገዙን አምራቾች ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።

ኢዜአ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምርትና አገልግሎታቸውን ይዘው የቀረቡ አምራቾችን ተዘዋውሮ አነጋግሯል።

የኢናስ ሶሊሽን ተወካይ ዮናስ ሸዋንግዛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የአምራች ኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግና በሥራ ዕድል ፈጠራ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል።

ፋብሪካቸው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚጠይቀውን ብረት በአገር ውስጥ በማምረት ተስፋ ሰጪ አቅም እየፈጠረ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የሸንጋይ ማሽነሪ ሥራ አስፈፃሚ ብርቱካን ጌታሁን በበኩላቸው ለኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከፍተኛ አቅም የሚሆኑ የግንባታ ማሽነሪ እያመረቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው የተሰጠው ትኩረት በተኪ ምርትና በስራ ዕድል ፈጠራ ገንቢ ሚና እንዲወጡ እያስቻላቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ኤክስፖው በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቁ የብረታ ብረት ውጤቶችን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር ለመፍጠር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የፔጋስ ኢንጂነሪንግ ተወካይ ሰለሞን ታደሰ ተናግረዋል።

ድርጅታቸው ከውጭ የሚገቡ የተሽከርካሪ አካላትን በሀገር ውስጥ በማምረት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀው በቀጣይም በተኪ ምርት ላይ በስፋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

የዲኬ ኦልድ ኩባንያ ተወካይ ወይዘሮ የምስራች ንጋቱ ኤክስፖው ምርትና አገልግሎታቸውን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር የሚያገኙበትን መልካም አጋጣሚ መፍጠሩን አስረድተዋል።

ንቅናቄው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለማምረት ከማስቻሉ በላይ ሰፊ የስራ ዕድል ለመፍጠር የራሱን ሚና መጫወቱን አስረድተዋል፡፡

መንግስት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ዘርፉን ለማበረታታት እያደረገ የሚገኘው ድጋፍና ክትትል የምርታማነት አቅማቸውን ለማሳደግ ከፍተኛ ዕገዛ እያደረገላቸው እንደሚገኝ አስተያየት ሰጪዎቹ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026