የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የአዲስ አበባን የልማትና የሰላም ምሳሌነት ለማስቀጠል የሰላም ሰራዊት አባላት ሚና የላቀ ነው-አቶ ሞገስ ባልቻ

May 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባን የልማትና የሰላም ምሳሌነት ለማስቀጠል የሰላም ሰራዊት አባላት የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ገለጹ፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ በተግባርና ንድፈ ሐሳብ ያሰለጠናቸውን 11 ሺህ ምልምል የሰላም ሰራዊት አባላት አስመርቋል።


በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ እንደገለጹት፤ በፓርቲው አመራርና የህዝቡ ተሳትፎ አዲስ አበባን ውብ፣ ጽዱ እና ዓለም-አቀፍ የከተማ ስታንዳርድ እንድታሟላ እየተደረገ ነው።


ፓርቲው ባለፉት የለውጥ ዓመታት በህዝብ የተጣለበትን ኃላፊነት እና የገባቸውን ቃሎች በተግባር በመፈጸም ህዝባዊ ወገንተኝነቱን በተግባር አሳይቷል ብለዋል፡፡


በመዲናዋ ለሰው ተኮር ተግባራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸው፥ የህዝቡ ተሳትፎ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


የመዲናዋን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ የሰላም ሰራዊት አባላት ከመደበኛ የፀጥታ ተቋማት ጋር እያደረጉት ያለው ቅንጅታዊ ስራ አበረታች እንደሆነም ተናግረዋል፡፡


በዚህም የፀረ ሰላም ኃይሎችን እኩይ ተግባር ቀድሞ ማክሽፍ እና ከምንጩ ማድረቅ መቻሉን ገልጸው፥ የዛሬ ተመራቂዎችም ከተማዋን የልማትና የሰላም ምሳሌ አድርጎ ማስቀጠል ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።


የአዲስ አበባ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው፤ የመዲናዋን ፈጣን እድገት ለማስቀጠል አስተማማኝ ሰላምን ማስፈን የግድ መሆኑን ገልጸዋል።


ከተማ አስተዳደሩ የህዝብን ቀጥተኛ ተሳትፎ ያረጋገጠ የሰላም ሰራዊት በመገንባት የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።


ዛሬ ከተረመቁ የሰላም ሰራዊት አባላት መካከል ሻለቃ ብርሐኑ በቀለ፥ በወሰዱት የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠና መሰረት አካባቢያቸውን በንቃት ለመጠበቅ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡


ሌላኛዋ ተመራቂ ትዕግስት አበጋዝ በበኩላቸው፥በስልጠና ቆይታቸው ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር ሰላምን ለማስጠበቅ የሚያስችል እውቀት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል፡፡


ለጸጥታ ኃይሉ አጋዥ ሆነን የአካባቢያችንን ሰላም ለማረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ ተዘጋጅተናል ያሉት ደግሞ አቶ ያለው ታደሰ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025