
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባን የልማትና የሰላም ምሳሌነት ለማስቀጠል የሰላም ሰራዊት አባላት የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ገለጹ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ በተግባርና ንድፈ ሐሳብ ያሰለጠናቸውን 11 ሺህ ምልምል የሰላም ሰራዊት አባላት አስመርቋል።
በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ እንደገለጹት፤ በፓርቲው አመራርና የህዝቡ ተሳትፎ አዲስ አበባን ውብ፣ ጽዱ እና ዓለም-አቀፍ የከተማ ስታንዳርድ እንድታሟላ እየተደረገ ነው።
ፓርቲው ባለፉት የለውጥ ዓመታት በህዝብ የተጣለበትን ኃላፊነት እና የገባቸውን ቃሎች በተግባር በመፈጸም ህዝባዊ ወገንተኝነቱን በተግባር አሳይቷል ብለዋል፡፡
በመዲናዋ ለሰው ተኮር ተግባራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸው፥ የህዝቡ ተሳትፎ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
የመዲናዋን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ የሰላም ሰራዊት አባላት ከመደበኛ የፀጥታ ተቋማት ጋር እያደረጉት ያለው ቅንጅታዊ ስራ አበረታች እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
በዚህም የፀረ ሰላም ኃይሎችን እኩይ ተግባር ቀድሞ ማክሽፍ እና ከምንጩ ማድረቅ መቻሉን ገልጸው፥ የዛሬ ተመራቂዎችም ከተማዋን የልማትና የሰላም ምሳሌ አድርጎ ማስቀጠል ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
የአዲስ አበባ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው፤ የመዲናዋን ፈጣን እድገት ለማስቀጠል አስተማማኝ ሰላምን ማስፈን የግድ መሆኑን ገልጸዋል።
ከተማ አስተዳደሩ የህዝብን ቀጥተኛ ተሳትፎ ያረጋገጠ የሰላም ሰራዊት በመገንባት የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
ዛሬ ከተረመቁ የሰላም ሰራዊት አባላት መካከል ሻለቃ ብርሐኑ በቀለ፥ በወሰዱት የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠና መሰረት አካባቢያቸውን በንቃት ለመጠበቅ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡
ሌላኛዋ ተመራቂ ትዕግስት አበጋዝ በበኩላቸው፥በስልጠና ቆይታቸው ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር ሰላምን ለማስጠበቅ የሚያስችል እውቀት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ለጸጥታ ኃይሉ አጋዥ ሆነን የአካባቢያችንን ሰላም ለማረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ ተዘጋጅተናል ያሉት ደግሞ አቶ ያለው ታደሰ ናቸው፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025