የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የአዲስ አበባን የልማትና የሰላም ምሳሌነት ለማስቀጠል የሰላም ሰራዊት አባላት ሚና የላቀ ነው-አቶ ሞገስ ባልቻ

May 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባን የልማትና የሰላም ምሳሌነት ለማስቀጠል የሰላም ሰራዊት አባላት የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ገለጹ፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ በተግባርና ንድፈ ሐሳብ ያሰለጠናቸውን 11 ሺህ ምልምል የሰላም ሰራዊት አባላት አስመርቋል።


በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ እንደገለጹት፤ በፓርቲው አመራርና የህዝቡ ተሳትፎ አዲስ አበባን ውብ፣ ጽዱ እና ዓለም-አቀፍ የከተማ ስታንዳርድ እንድታሟላ እየተደረገ ነው።


ፓርቲው ባለፉት የለውጥ ዓመታት በህዝብ የተጣለበትን ኃላፊነት እና የገባቸውን ቃሎች በተግባር በመፈጸም ህዝባዊ ወገንተኝነቱን በተግባር አሳይቷል ብለዋል፡፡


በመዲናዋ ለሰው ተኮር ተግባራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸው፥ የህዝቡ ተሳትፎ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


የመዲናዋን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ የሰላም ሰራዊት አባላት ከመደበኛ የፀጥታ ተቋማት ጋር እያደረጉት ያለው ቅንጅታዊ ስራ አበረታች እንደሆነም ተናግረዋል፡፡


በዚህም የፀረ ሰላም ኃይሎችን እኩይ ተግባር ቀድሞ ማክሽፍ እና ከምንጩ ማድረቅ መቻሉን ገልጸው፥ የዛሬ ተመራቂዎችም ከተማዋን የልማትና የሰላም ምሳሌ አድርጎ ማስቀጠል ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።


የአዲስ አበባ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው፤ የመዲናዋን ፈጣን እድገት ለማስቀጠል አስተማማኝ ሰላምን ማስፈን የግድ መሆኑን ገልጸዋል።


ከተማ አስተዳደሩ የህዝብን ቀጥተኛ ተሳትፎ ያረጋገጠ የሰላም ሰራዊት በመገንባት የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።


ዛሬ ከተረመቁ የሰላም ሰራዊት አባላት መካከል ሻለቃ ብርሐኑ በቀለ፥ በወሰዱት የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠና መሰረት አካባቢያቸውን በንቃት ለመጠበቅ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡


ሌላኛዋ ተመራቂ ትዕግስት አበጋዝ በበኩላቸው፥በስልጠና ቆይታቸው ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር ሰላምን ለማስጠበቅ የሚያስችል እውቀት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል፡፡


ለጸጥታ ኃይሉ አጋዥ ሆነን የአካባቢያችንን ሰላም ለማረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ ተዘጋጅተናል ያሉት ደግሞ አቶ ያለው ታደሰ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026