አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2017(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች የሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ቁጥር እየጨመረ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በክልሉ በርካታ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በመለየት ወደ ስራ ተገብቷል።
ከተለዩት የኢንቨስትመንት አማራጮች መካከልም የተለያዩ የተፈጥሮ ማዕድናት ሀብቶች ተጠቃሽ ናቸው።
ይህንንም ተከትሎ ኢንቨስተሮች በክልሉ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ አመልክተዋል፡፡
በዚህም የሀገር ውስጥና የውጭ ኢንቨስተሮች በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች እየተሰማሩ መሆኑንና በተሰማሩበት ዘርፍም ውጤታማ እየሆኑ እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡
ከክልሉ የተለያዩ ምርቶች ወደ ውጭ እየተላኩ መሆኑን አንስተው፤ የኮፐር ማዕድን ምርት በሙከራ ደረጃ ወደ ውጭ መላክ መጀመሩን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በቀጣይም ሌሎች ምርቶችን ለመላክ እየተሰራ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጨምረው አስታውቀዋል፡፡
ከ10 በላይ የውጭ ካምፓኒዎች በግብርና ልማት፣ በሪል ስቴት ግንባታ፣ በኬሚካል ኢንዱስትሪ እና በሌሎች የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውንም ተናግረዋል።
በክልሉ የኮሪደር ልማት መጀመሩ ኢንቨስትመንት በመሳብ ረገድ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑንና ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በክልሉ የሚገኙ ጸጋዎችን የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝና ህብረተሰቡን ከኢንቨስትመንቱ ተጠቃሚ በማድረግ በኩል ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025