
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2017(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች የሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ቁጥር እየጨመረ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በክልሉ በርካታ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በመለየት ወደ ስራ ተገብቷል።
ከተለዩት የኢንቨስትመንት አማራጮች መካከልም የተለያዩ የተፈጥሮ ማዕድናት ሀብቶች ተጠቃሽ ናቸው።
ይህንንም ተከትሎ ኢንቨስተሮች በክልሉ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ አመልክተዋል፡፡
በዚህም የሀገር ውስጥና የውጭ ኢንቨስተሮች በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች እየተሰማሩ መሆኑንና በተሰማሩበት ዘርፍም ውጤታማ እየሆኑ እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡
ከክልሉ የተለያዩ ምርቶች ወደ ውጭ እየተላኩ መሆኑን አንስተው፤ የኮፐር ማዕድን ምርት በሙከራ ደረጃ ወደ ውጭ መላክ መጀመሩን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በቀጣይም ሌሎች ምርቶችን ለመላክ እየተሰራ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጨምረው አስታውቀዋል፡፡
ከ10 በላይ የውጭ ካምፓኒዎች በግብርና ልማት፣ በሪል ስቴት ግንባታ፣ በኬሚካል ኢንዱስትሪ እና በሌሎች የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውንም ተናግረዋል።
በክልሉ የኮሪደር ልማት መጀመሩ ኢንቨስትመንት በመሳብ ረገድ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑንና ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በክልሉ የሚገኙ ጸጋዎችን የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝና ህብረተሰቡን ከኢንቨስትመንቱ ተጠቃሚ በማድረግ በኩል ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025