የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በአፋር ክልል በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ የኢንቨስተሮች ቁጥር እየጨመረ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

May 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2017(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች የሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ቁጥር እየጨመረ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በክልሉ በርካታ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በመለየት ወደ ስራ ተገብቷል።

ከተለዩት የኢንቨስትመንት አማራጮች መካከልም የተለያዩ የተፈጥሮ ማዕድናት ሀብቶች ተጠቃሽ ናቸው።

ይህንንም ተከትሎ ኢንቨስተሮች በክልሉ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ አመልክተዋል፡፡

በዚህም የሀገር ውስጥና የውጭ ኢንቨስተሮች በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች እየተሰማሩ መሆኑንና በተሰማሩበት ዘርፍም ውጤታማ እየሆኑ እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡

ከክልሉ የተለያዩ ምርቶች ወደ ውጭ እየተላኩ መሆኑን አንስተው፤ የኮፐር ማዕድን ምርት በሙከራ ደረጃ ወደ ውጭ መላክ መጀመሩን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በቀጣይም ሌሎች ምርቶችን ለመላክ እየተሰራ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጨምረው አስታውቀዋል፡፡

ከ10 በላይ የውጭ ካምፓኒዎች በግብርና ልማት፣ በሪል ስቴት ግንባታ፣ በኬሚካል ኢንዱስትሪ እና በሌሎች የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውንም ተናግረዋል።

በክልሉ የኮሪደር ልማት መጀመሩ ኢንቨስትመንት በመሳብ ረገድ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑንና ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በክልሉ የሚገኙ ጸጋዎችን የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝና ህብረተሰቡን ከኢንቨስትመንቱ ተጠቃሚ በማድረግ በኩል ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025