አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ በወሰደቻቸው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማሳካት በትክክለኛ መንገድ ላይ እንደምትገኝ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ።
በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በፎረሙ መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ በርካታ የለውጥ እርምጃ እየወሰደች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎችም እድገትን ለማስቀጠል፣የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እና መዋቅራዊ ሽግግርን ለማሳካት እንደሚያስችሉ ተናግረዋል።
ይህም ኢትዮጵያ በትክክለኛው የዕድገት ጎዳና ላይ እንድትገኝ አድርጓታል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ብሩህ መሆኑን ገልጸዋል።
የማበረታቻ ስርዓቶችም ባለሀብቶች ኢንቨስትመንታቸውን እንዲያስፋፉና ዘላቂነትን እንዲያረጋግጡ የሚያግዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ፎረሙ ኢትዮጵያ ያላትን የኢንቨስትመንት አቅም ለማሳየት ትልቅ ዕድል መሆኑን ጠቅሰው፤ የመድረኩ ተሳታፊዎች የተሻሉ ልምዶችን እንዲለዋወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ ከውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት የተሻለ አድል ለማግኘት በሶስት መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ማድረጓን ገልጸዋል።
ለውጭ ባለሀብቶች ዝግ ሆነው የቆዩ ዘርፎችን የመክፈት ሀገራዊ ሪፎርም፣ የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎች እና በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ ተጨባጭ ለውጦች ማምጣታቸውን አንስተዋል።
እንዲሁም ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆኑ መሰረተ ልማቶች እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው መስኮች ለሚሰማሩ በርካታ ማሻሻያዎችን ማድረጓን ጠቁመዋል።
በብዙ የበለጸጉ አገራት የውጭ ባለሀብቶች ስኬት በሦስት ምክንያቶች ላይ ብቻ ያተኮረ መሆኑን አንስተዋል።
ይህም የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ እውቀት መስፋፋት እና የገበያ ትስስር መሆኑን ገልጸው፤ የኢትዮጵያ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ከአህጉራዊና ዓለምአቀፋዊ የአቅርቦት ሰንሰለት ጋር ማቀናጀት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ይህም ኢንቨስተሮች የረጅም ጊዜ እና ዘላቂ ኢንቨስትመንትን ለማረጋገጥ በጣም ወሳኝ መሆኑንም አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025