የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የቱሪስት መስህብ ቦታዎችን በማልማት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው - ቋሚ ኮሚቴው

May 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ ነባርና አዳዲስ የቱሪስት መስህቦችን በማልማት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ።

ቋሚ ኮሚቴው የቱሪዝም ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።

በግምገማው ከቱሪስት መዳረሻ ልማት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራና ጎብኚዎችን የመሳብ ሥራዎች ዙሪያ ትኩረት ያደረጉ ጥያቄዎች ቀርበው በሚኒስቴሩ የሥራ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።


የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ የውጭ ጎብኚዎችን ቁጥር አንድ ሚሊዮን ለማደረስ ግብ ተጥሎ ርብርብ ተደርጓል።

በዚህም በዘጠኝ ወራት በተከናወኑ ተግባራት 942ሺህ 407 ጎብኚዎች መምጣታቸውን ጠቁመው፤ ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ አፈጻጸም የተመዘገበበት ነው ብለዋል።

ለ100ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ከ80ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በሆቴሎች፣ በቱሪስት መዳረሻ ቦታዎች፣ በአስጎብኚ ድርጅቶች የሥራ ዕድል መፈጠሩንም አብራርተዋል።


በበጀት ዓመቱ የሆቴሎችን ደረጃ የመመደብ ተግባራት መከናወናቸውንም ጨምረው ተናግረዋል።

ለባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና በመስጠት ወደ ሥራ የማስገባቱ ሥራም ቀጣይነት ባለው መልኩ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ ያላትን እምቅ ሃብት በተለያዩ አማራጮች የማስተዋወቅ ተግባራት በሰፊው እየተከናወኑ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ከውጭ ምንዛሬ ግኝት አኳያም ዘርፉ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ እያደገ ሲሆን፤ በቀጣይም የውጭ ምንዛሬ ግኝቱን ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።


የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፤ ሚኒስቴሩ የቱሪስት መስህብ ቦታዎችን ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው።

ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር ብሄራዊ ፓርኮች የውስጥ ለውስጥ መንገዶች እየተገነባላቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበርም የኔት ወርክ አገልግሎት የሌለባቸው መዳረሻዎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።


የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የውጭ ጎብኚዎችን ፍሰት መጨመር የሚያስችል ስትራቴጂ ተነድፎ ወደ ሥራ መገባቱን አብራርተዋል።

በዚህም በመካከለኛው ምስራቅ እንዲሁም ላቲን አሜሪካ ሀገራት ጎብኚዎችን ለመሳብ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ነው ያሉት።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አይሻ ያህያ እንዳሉት፤ ነባርና አዳዲስ የቱሪስት መስህቦችን በማልማት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።

በቱሪዝም ዘርፍ ኢንቨስትመንት የመሳብ ሥራ በትኩረት ሊከናወን እንደሚገባ ጠቁመው፤ እምቅ ሃብቶችን ይበልጥ በማስተዋወቅ ከዘርፉ የተሻለ ጥቅም እንዲገኝ መሥራት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026