የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የአምራች ዘርፉን እንቅስቃሴ በመደገፍና በማገዝ የተኪ ምርት አቅርቦትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ይጠናከራል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)

May 15, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ የአምራች ዘርፉን እንቅስቃሴ በመደገፍና በማገዝ የተኪ ምርት አቅርቦትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

በክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተዘጋጀ የማኑፋክቸሪንግ ውጤቶች ባዛርና ኤግዚቢሽን በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡

በዚሁ መርሃ ግብር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር )፤ በክልሉ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ስኬታማ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።


ዘርፉ ተኪ ምርቶችን በስፋት በማምረት ኢኮኖሚውን ለመደገፍና የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመቀነስ ጉልህ ድርሻ ያለው መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም የአምራች ዘርፉን እንቅስቃሴ በመደገፍና በማገዝ የተኪ ምርት አቅርቦትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ታምራት ንቅናቄ በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች ስራ ያቆሙ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲነቃቁ ማድረጉን ጠቁመው በዚህም በርካታ ኢንዱስትሪዎች ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

በክልሉ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን በማጠናከር ሁሉ አቀፍ ውጤት ለማስመዝገብ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የኮርፖሬሽኑ ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ስንታየሁ ወልደ ሚካኤል፤ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለዘርፉ መነሳሳት የላቀ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።

በመሆኑም ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የገበያ ትስስር በመፍጠር የምርት ሂደቱን ለማሳለጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ናትናኤል ሚሊየን በበኩላቸው ኮርፖሬሽኑ ተኪ ምርቶችን በማምረት የክልሉን ገቢ ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል፡፡

ኢንዱስትሪዎቹ የግብርና ምርቶች ላይ ዕሴት በመጨመር በኩል አበረታች እንቅስቃሴ ላይ የሚገኙ ሲሆን ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026