
ሆሳዕና፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ የአምራች ዘርፉን እንቅስቃሴ በመደገፍና በማገዝ የተኪ ምርት አቅርቦትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ፡፡
በክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተዘጋጀ የማኑፋክቸሪንግ ውጤቶች ባዛርና ኤግዚቢሽን በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡
በዚሁ መርሃ ግብር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር )፤ በክልሉ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ስኬታማ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

ዘርፉ ተኪ ምርቶችን በስፋት በማምረት ኢኮኖሚውን ለመደገፍና የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመቀነስ ጉልህ ድርሻ ያለው መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም የአምራች ዘርፉን እንቅስቃሴ በመደገፍና በማገዝ የተኪ ምርት አቅርቦትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ታምራት ንቅናቄ በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች ስራ ያቆሙ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲነቃቁ ማድረጉን ጠቁመው በዚህም በርካታ ኢንዱስትሪዎች ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
በክልሉ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን በማጠናከር ሁሉ አቀፍ ውጤት ለማስመዝገብ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የኮርፖሬሽኑ ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ስንታየሁ ወልደ ሚካኤል፤ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለዘርፉ መነሳሳት የላቀ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።
በመሆኑም ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የገበያ ትስስር በመፍጠር የምርት ሂደቱን ለማሳለጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ናትናኤል ሚሊየን በበኩላቸው ኮርፖሬሽኑ ተኪ ምርቶችን በማምረት የክልሉን ገቢ ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል፡፡
ኢንዱስትሪዎቹ የግብርና ምርቶች ላይ ዕሴት በመጨመር በኩል አበረታች እንቅስቃሴ ላይ የሚገኙ ሲሆን ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025