
ነቀምቴ፤ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦በነቀምቴ ከተማ በ464 ሚሊዮን ብር እየተካሄዱ የሚገኙ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የከተማዋ ማዘጋጃ ቤት ገለፀ።
የከተማዋ ማዘጋጃ ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የመሰረተ ልማት ስራዎች ቡድን መሪ አቶ ደረጄ ዶጃ እንደገለጹት በከተማው ነዋሪውን ተጠቃሚ ያደረጉ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።
በተያዘው በጀት ዓመትም 37 የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ በ464 ሚሊዮን ብር እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
ከልማት ስራዎቹ መካከል የኮብልስቶን ድንጋይ ንጣፍ እና እድሳት፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቦዮች፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታና ከፈታ፣ የመንገድ ዳር መብራቶች ተከላ፣ የውሃ መስመር ዝርጋታ እና ሌሎች ስራዎች ይገኙበታል ብለዋል።
ከግብርና ኢኒሼቲቭ አንጻርም ለከብት ለማደለብ፣ ለዶሮ እርባታ፣ ለወተት ላሞች እርባታ፣ ለጎጆ ኢንዱስትሪ እና ለመኖ ማዘጋጃ የሚውሉ ሼዶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑንም ተናግረዋል።
የመሰረተ ልማት ስራዎቹ ሲጠናቀቁ በርካታ የከተማዋን ነዋሪዎች ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሲሆን ለበርካታ ወጣቶችም የስራ እድል መፍጠራቸውን ጠቅሰዋል።
ከግንባታ ሂደቱም ባለፈ በከተማዋ በተገነቡ የዶሮ እርባታ እና የበሬ ማደለቢያ ሼዶች ወጣቶች ተደራጅተው የስራ እድል ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
በግንባታ ላይ የመሚገኙ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች አብዛኞች መጠናቀቃቸውን ገልጸው ቀሪዎቹን የበጀት ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት አጠናቆ ለህዝብ አገልግሎት ለማዋል ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በከተማው በተገነቡ ሼዶች የስራ እድል ከተፈጠረላቸው መካከል የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ መደበኛ ህይወት የተቀላቀሉ ወጣቶች ይገኙበታል።
ከነዚህም መካከል ወጣት ደበላ መርጋ፤ ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር በማህበር በመደራጀት በዶሮ እርባታ ስራ ላይ መሰማራታቸውን ገልጿል።
ለዚህም ከከተማ አስተዳደሩ ከገንዘብ ጀምሮ አስፈላጊ ድጋፍ ማግኘታቸውን ጠቁሞ ባገኙት ሰርተው ለመለወጥ እየተጉ መሆኑን ተናግሯል።
በተመሳሳይም የተሃድሶ ስልጠና ወስዶ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ኬንቦን ቀነአ፤ ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር በመሆን ከብት በማደለብ ስራ ላይ መሰማራቱን ይናገራል።
በቀጣይም ባገኙት እድል የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆንና ህይወታቸውን ለመቀየር እንደሚተጉም ጠቁሟል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026