አዲስ አበባ፤ግንቦት 10/2017 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ኮንፈረንሶችን የማዘጋጀት እቅም እያደገ መምጣቱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ ዓለም ዓቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖን(ETEX 2025) ጎብኝተዋል።
ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት፤ ከተማዋ ከአገር አልፎ የዓለም አቀፍ እና አህጉረ አቀፍ ኮንፈረንስ የማዘጋጀት አቅም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
በመዲናዋ እየተካሄዱ የሚገኙ ኮንፈረንሶች የከተማዋን ገቢ እንዲጨምር ማድረጉን ጠቁመው፤ የኮንፈረንስ እና የቱሪዝም መዳረሻነቷን ከማሳደግ በላይ በርካታ የሥራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
ባለፉት አስር ቀናት ብቻ በርካታ ኮንፈረንስ እና ኤክስፖዎች መካሄዳቸውን ገልፀው፤ ይህም የከተማዋን ገቢ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
በአገሪቷ በቴክኖሎጂ ልማት ከፍተኛ ለውጥ እና እድገት እየተመዘገቡ ይገኛሉም ብለዋል።
መዲናዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ከንቲባ አዳነች ገልጸዋል።
ኤክስፖው ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማረጋገጥ የተያዘው ግብ ለማሳካት ጫፍ ላይ ስለመድረሳችን አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ሃይል ለማፍራትና የተፈጠረው አቅም የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥ በሚያስችል መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በከተማዋ ሁሉን አቀፍ የተሟላ የኮሪደር ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አውስተው፤ ከተማዋን የማዘመንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የመዘርጋት ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025