የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የአዲስ አበባ ከተማ ዓለምአቀፍ እና አህጉር አቀፍ ኮንፈረንሶችን የማዘጋጀት እቅም እያደገ መጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

May 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 10/2017 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ኮንፈረንሶችን የማዘጋጀት እቅም እያደገ መምጣቱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ ዓለም ዓቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖን(ETEX 2025) ጎብኝተዋል።

ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት፤ ከተማዋ ከአገር አልፎ የዓለም አቀፍ እና አህጉረ አቀፍ ኮንፈረንስ የማዘጋጀት አቅም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።

በመዲናዋ እየተካሄዱ የሚገኙ ኮንፈረንሶች የከተማዋን ገቢ እንዲጨምር ማድረጉን ጠቁመው፤ የኮንፈረንስ እና የቱሪዝም መዳረሻነቷን ከማሳደግ በላይ በርካታ የሥራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለፉት አስር ቀናት ብቻ በርካታ ኮንፈረንስ እና ኤክስፖዎች መካሄዳቸውን ገልፀው፤ ይህም የከተማዋን ገቢ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

በአገሪቷ በቴክኖሎጂ ልማት ከፍተኛ ለውጥ እና እድገት እየተመዘገቡ ይገኛሉም ብለዋል።

መዲናዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ከንቲባ አዳነች ገልጸዋል።

ኤክስፖው ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማረጋገጥ የተያዘው ግብ ለማሳካት ጫፍ ላይ ስለመድረሳችን አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ሃይል ለማፍራትና የተፈጠረው አቅም የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥ በሚያስችል መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በከተማዋ ሁሉን አቀፍ የተሟላ የኮሪደር ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አውስተው፤ ከተማዋን የማዘመንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የመዘርጋት ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025