
አዲስ አበባ፤ግንቦት 10/2017 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ኮንፈረንሶችን የማዘጋጀት እቅም እያደገ መምጣቱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ ዓለም ዓቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖን(ETEX 2025) ጎብኝተዋል።
ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት፤ ከተማዋ ከአገር አልፎ የዓለም አቀፍ እና አህጉረ አቀፍ ኮንፈረንስ የማዘጋጀት አቅም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
በመዲናዋ እየተካሄዱ የሚገኙ ኮንፈረንሶች የከተማዋን ገቢ እንዲጨምር ማድረጉን ጠቁመው፤ የኮንፈረንስ እና የቱሪዝም መዳረሻነቷን ከማሳደግ በላይ በርካታ የሥራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
ባለፉት አስር ቀናት ብቻ በርካታ ኮንፈረንስ እና ኤክስፖዎች መካሄዳቸውን ገልፀው፤ ይህም የከተማዋን ገቢ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
በአገሪቷ በቴክኖሎጂ ልማት ከፍተኛ ለውጥ እና እድገት እየተመዘገቡ ይገኛሉም ብለዋል።
መዲናዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ከንቲባ አዳነች ገልጸዋል።
ኤክስፖው ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማረጋገጥ የተያዘው ግብ ለማሳካት ጫፍ ላይ ስለመድረሳችን አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ሃይል ለማፍራትና የተፈጠረው አቅም የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥ በሚያስችል መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በከተማዋ ሁሉን አቀፍ የተሟላ የኮሪደር ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አውስተው፤ ከተማዋን የማዘመንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የመዘርጋት ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025