የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኤክስፖ 2025 ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ እያከናወነች ያለችውን ውጤታማ ተግባራት ያሳየችበት ነው

May 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 10/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የተካሄደው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ እያከናወነች ያለችውን ውጤታማ ተግባራት ያሳየችበት መሆኑ ተገለፀ።

በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 ተጠናቋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሀሚድ እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) የኤክስፖውን መጠናቀቅ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም፥ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በዲጂታላይዜሽን እና በቴክኖሎጂ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለዓለም ማስተዋወቅና በርካታ ትስስር መፍጠር ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሀሚድ፥ በኤክስፖው ከ15 ሺህ በላይ ታዳሚዎች መሣተፋቸውን ተናግረዋል።

ኤክስፖ 2025 የሳይበር ደህንነት፣ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የፋይናንስ ደህንነት፣ ስማርት ሲቲ እና የቴክኖሎጂ ትምህርት ዘርፎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

በዓይነቱ ልዩ በሆነው ኤክስፖ 2025 ከመንግሥት፣ ከግል እና ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወጣጡ ኩባንያዎች መሣተፋቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኤክስፖ 2025 በርካታ ወጣቶች እንዲነቃቁ ያደረገ ነው ብለዋል።

ከ100 በላይ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በኤክስፖ 2025 መሣተፋቸውን ጠቁመው፤ የተለያዩ ውድድሮች ተካሂደው ኢትዮጵያውያን ማሸነፋቸውን ተናግረዋል።

ኤክስፖው ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያለችበትን ደረጃ ያሳየችበት መሆኑንም ጠቁመዋል።

ዓለም አቀፍ ኤክስፖ 2025 ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ እያከናወነች ያለችውን ውጤታማ ተግባራት ያሳየችበት መሆኑንም ተናግረዋል።

ኤክስፖው ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ያስመዘገበቻቸው ስኬቶችን እና በዲጂታል ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለዓለም ያስተዋወቀችበት ነውም ተብሏል።

በኤክስፖው የተለያዩ ጥናቶች የቀረቡበት፣ የፓናል ውይይቶች እንዲሁም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሮቦቲክስ ውድድሮች የተካሄዱበት ነበር።

ይህ በኢትዮጵያ የተሰናዳው ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በሁሉም መስክ የምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የቴክኖሎጂ ሁነት ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026