የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኤክስፖ 2025 ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ እያከናወነች ያለችውን ውጤታማ ተግባራት ያሳየችበት ነው

May 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 10/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የተካሄደው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ እያከናወነች ያለችውን ውጤታማ ተግባራት ያሳየችበት መሆኑ ተገለፀ።

በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 ተጠናቋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሀሚድ እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) የኤክስፖውን መጠናቀቅ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም፥ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በዲጂታላይዜሽን እና በቴክኖሎጂ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለዓለም ማስተዋወቅና በርካታ ትስስር መፍጠር ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሀሚድ፥ በኤክስፖው ከ15 ሺህ በላይ ታዳሚዎች መሣተፋቸውን ተናግረዋል።

ኤክስፖ 2025 የሳይበር ደህንነት፣ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የፋይናንስ ደህንነት፣ ስማርት ሲቲ እና የቴክኖሎጂ ትምህርት ዘርፎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

በዓይነቱ ልዩ በሆነው ኤክስፖ 2025 ከመንግሥት፣ ከግል እና ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወጣጡ ኩባንያዎች መሣተፋቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኤክስፖ 2025 በርካታ ወጣቶች እንዲነቃቁ ያደረገ ነው ብለዋል።

ከ100 በላይ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በኤክስፖ 2025 መሣተፋቸውን ጠቁመው፤ የተለያዩ ውድድሮች ተካሂደው ኢትዮጵያውያን ማሸነፋቸውን ተናግረዋል።

ኤክስፖው ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያለችበትን ደረጃ ያሳየችበት መሆኑንም ጠቁመዋል።

ዓለም አቀፍ ኤክስፖ 2025 ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ እያከናወነች ያለችውን ውጤታማ ተግባራት ያሳየችበት መሆኑንም ተናግረዋል።

ኤክስፖው ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ያስመዘገበቻቸው ስኬቶችን እና በዲጂታል ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለዓለም ያስተዋወቀችበት ነውም ተብሏል።

በኤክስፖው የተለያዩ ጥናቶች የቀረቡበት፣ የፓናል ውይይቶች እንዲሁም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሮቦቲክስ ውድድሮች የተካሄዱበት ነበር።

ይህ በኢትዮጵያ የተሰናዳው ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በሁሉም መስክ የምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የቴክኖሎጂ ሁነት ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025