የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በመስኖ ታግዘን ከምናከናውነው የግብርና ሥራ ውጤታማ ለመሆን ጠንክረን እየሰራን ነው-አርሶ አደሮች

May 19, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦በአካባቢያቸው በተገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች ታግዘው ከሚያከናውኑ የግብርና ሥራ ውጤታማ ለመሆን ተግተው እየሰሩ መሆኑን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጉራጌ እና የየም ዞኖች አርሶ አደሮች ገለጹ።


አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ አርሶ አደሮች መካከል በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ጌታቸው ፈቀደ በአካባቢው በመንግስት ድጋፍ የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት የግብርና ምርታማነታቸውን በማሳደግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዕድል ፈጥሯል።


ቀደም ሲል ከወንዝ ውሃ በጄኔሬተር ስበው ሲያለሙ ለብዙ ወጪና ብክነት ሲዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል።


መንግስት የገነባው የሬቡ መስኖ ፕሮጀክት በአካባቢያቸው አቋርጦ ስለሚያልፍ ውሃውን ጠልፈው የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ጠንክረው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።


ለግብርና ስራችን ከመስኖ በተጨማሪ አማራጭ ቴክኖሎጂዎች መንግስት ማመቻቸቱ ልማቱን በተሻለ ለማከናወን አነሳስቶናል" ያሉት ደግሞ ሌላኛው የወረዳው አርሶ አደር ኑርአዲስ ሁሴን ናቸው።


ለመስኖ ግንባታ የሚሆን የወንዝ አማራጭ በሌለባቸው አካባቢዎች መንግስት በፀሐይ ሀይል የሚሰራ የውሃ መሳቢያ ሞተር በማምቻቸቱ የግብርና ሥራቸውን አስፋፍተው ለማከናወነ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።


በየም ዞን ደሪ ሳጃ ዙርያ ወረዳ የኮሻ መስኖን በመጠቀም በዓመት ሦስት ጊዜ እና ከዚያ በላይ ማምረት መጀመራቸውን የተናገሩት ደግሞ አርሶ አደር አጥናፉ ወልደኢየሱስ ናቸው።


ከዚህ ቀደም ሥራ በማጣት ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ሲዳረጉ እንደነበር አስታውሰው በአሁኑ ወቅት መስኖ በመጠቀም ማሽላ፣ በቆሎ፣ አትክልት እና ፍራፍሬ እያለሙ መሆናቸውንና የተሻለ ገቢ ለማግኘት ጠንክረው እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።


ሌላኛው አርሶ አደር ዘሪሁን ጋሼ መስኖን ጨምሮ በዓመት ከሦስት ጊዜ በላይ አትክልትና ፍራፍሬ በማምረትና ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።


ከዚህ በተጨማሪ በአጠገባቸው የሚያልፈውን የመስኖ ውሃ ተጠቅመው በሚያዘጋጁት ኩሬ ዓሣ ለማምረት ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ካሳዬ ተክሌ እንዳሉት ፣ በክልሉ በበጀት ዓመቱ ከ393 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ 16 አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።


እስካሁንም 10 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ሙሉ በሙሉ ለአገልግሎት መብቃታቸውን ጠቅሰው፣ ከወንዝ መጥለፍ ለማይችሉ አካባቢዎች በጸሐይ ሀይል የሚሰሩ 70 የውሃ መሳቢያ ሞተሮች መቅረባቸውን ጠቁመዋል።


በክልሉ ያለውን የውሃና የመሬት ሀብት በአግባቡ በመጠቀም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰው፣ በዚህም አርሶ አደሩ ከመነቃቃት ባለፈ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል።


የመስኖ ተቋማት በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻልም ከማህበረሰቡ ጋር በመወያየት የአጠቃቀም መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደስራ መገባቱን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026