ባህር ዳር፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የባህርዳር ከተማን ሰላም ለመጠበቅና የተረጋጋ ግብይት እንዲኖር ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ የከተማዋ ነጋዴዎች ተናገሩ።
"የጥፋት እጆቹና መዘዞቹ " በሚል መሪ ሃሳብ ከባህር ዳር ከተማ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ጋር ዛሬ የውይይት መድረክ ተካሄዷል።
የውይይቱ ተሳታፊ ነጋዴ ወይዘሮ ዘነበች መንግስቴ፤ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።
ይህም በሸማቹ ህብረተሰብ ላይ ችግር እየፈጠረ እንደሚገኝ ጠቁመው፥ መፍትሄ ለመሻት እየተደረገ ባለው ጥረት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡም ተናግረዋል።
ሌላኛዋ የሸቀጣ ሸቀጥ ነጋዴ ወጣት ምሳነሽ እናናው፤ የጽንፈኝነት አስተሳሰብን መከላከል የንግዱ ማህበረሰብን ጨምሮ የሁሉም ህብረተሰብ ኃላፊነት መሆን እንዳለበት ገልጻለች።
በዚህም የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ራስን መፈተሽና ከጽንፈኝነት አስተሳሰብ ከማውጣት በዘለለ በተሳሳተ መንገድ ውስጥ ያሉ ወገኖችን መምከር ይጠበቅበታል ብለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የባህር ዳር ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ብርሃን ንጉሴ በሰጡት ማብራሪያ፥ የጽንፈኝነት አስተሳሰብ የወለደው የሰላም እጦት በክልሉ ተጽእኖ አሳድሯል።
ይህም የንግዱ ማህበረሰብ ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ ስራውን እንደልቡ እንዳይሰራና ተረጋግቶ እንዳይኖር በማድረጉ በሸማቹ ላይም ተጽእኖው እንዲኖር አድርጓል ብለዋል።
የንግዱ ማህበረሰብም መንግስት ችግሩን በውይይትና በንግግር ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት ማገዝና መደገፍ ይጠበቅበታል ብለዋል።
በተጨማሪም የንግዱ ማህበረሰብ ጽንፈኞችን በማጋለጥ ለህግ የበላይነት መረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚጠበቅበትም አሳስበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025