የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ለከተማዋ ሰላም መጠበቅና ለተረጋጋ ገበያ መኖር የድርሻችንን እንወጣለን

May 19, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የባህርዳር ከተማን ሰላም ለመጠበቅና የተረጋጋ ግብይት እንዲኖር ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ የከተማዋ ነጋዴዎች ተናገሩ።


"የጥፋት እጆቹና መዘዞቹ " በሚል መሪ ሃሳብ ከባህር ዳር ከተማ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ጋር ዛሬ የውይይት መድረክ ተካሄዷል።


የውይይቱ ተሳታፊ ነጋዴ ወይዘሮ ዘነበች መንግስቴ፤ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።


ይህም በሸማቹ ህብረተሰብ ላይ ችግር እየፈጠረ እንደሚገኝ ጠቁመው፥ መፍትሄ ለመሻት እየተደረገ ባለው ጥረት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡም ተናግረዋል።


ሌላኛዋ የሸቀጣ ሸቀጥ ነጋዴ ወጣት ምሳነሽ እናናው፤ የጽንፈኝነት አስተሳሰብን መከላከል የንግዱ ማህበረሰብን ጨምሮ የሁሉም ህብረተሰብ ኃላፊነት መሆን እንዳለበት ገልጻለች።


በዚህም የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ራስን መፈተሽና ከጽንፈኝነት አስተሳሰብ ከማውጣት በዘለለ በተሳሳተ መንገድ ውስጥ ያሉ ወገኖችን መምከር ይጠበቅበታል ብለዋል።


በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የባህር ዳር ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ብርሃን ንጉሴ በሰጡት ማብራሪያ፥ የጽንፈኝነት አስተሳሰብ የወለደው የሰላም እጦት በክልሉ ተጽእኖ አሳድሯል።


ይህም የንግዱ ማህበረሰብ ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ ስራውን እንደልቡ እንዳይሰራና ተረጋግቶ እንዳይኖር በማድረጉ በሸማቹ ላይም ተጽእኖው እንዲኖር አድርጓል ብለዋል።


የንግዱ ማህበረሰብም መንግስት ችግሩን በውይይትና በንግግር ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት ማገዝና መደገፍ ይጠበቅበታል ብለዋል።


በተጨማሪም የንግዱ ማህበረሰብ ጽንፈኞችን በማጋለጥ ለህግ የበላይነት መረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚጠበቅበትም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026