የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ለከተማዋ ሰላም መጠበቅና ለተረጋጋ ገበያ መኖር የድርሻችንን እንወጣለን

May 19, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የባህርዳር ከተማን ሰላም ለመጠበቅና የተረጋጋ ግብይት እንዲኖር ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ የከተማዋ ነጋዴዎች ተናገሩ።


"የጥፋት እጆቹና መዘዞቹ " በሚል መሪ ሃሳብ ከባህር ዳር ከተማ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ጋር ዛሬ የውይይት መድረክ ተካሄዷል።


የውይይቱ ተሳታፊ ነጋዴ ወይዘሮ ዘነበች መንግስቴ፤ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።


ይህም በሸማቹ ህብረተሰብ ላይ ችግር እየፈጠረ እንደሚገኝ ጠቁመው፥ መፍትሄ ለመሻት እየተደረገ ባለው ጥረት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡም ተናግረዋል።


ሌላኛዋ የሸቀጣ ሸቀጥ ነጋዴ ወጣት ምሳነሽ እናናው፤ የጽንፈኝነት አስተሳሰብን መከላከል የንግዱ ማህበረሰብን ጨምሮ የሁሉም ህብረተሰብ ኃላፊነት መሆን እንዳለበት ገልጻለች።


በዚህም የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ራስን መፈተሽና ከጽንፈኝነት አስተሳሰብ ከማውጣት በዘለለ በተሳሳተ መንገድ ውስጥ ያሉ ወገኖችን መምከር ይጠበቅበታል ብለዋል።


በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የባህር ዳር ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ብርሃን ንጉሴ በሰጡት ማብራሪያ፥ የጽንፈኝነት አስተሳሰብ የወለደው የሰላም እጦት በክልሉ ተጽእኖ አሳድሯል።


ይህም የንግዱ ማህበረሰብ ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ ስራውን እንደልቡ እንዳይሰራና ተረጋግቶ እንዳይኖር በማድረጉ በሸማቹ ላይም ተጽእኖው እንዲኖር አድርጓል ብለዋል።


የንግዱ ማህበረሰብም መንግስት ችግሩን በውይይትና በንግግር ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት ማገዝና መደገፍ ይጠበቅበታል ብለዋል።


በተጨማሪም የንግዱ ማህበረሰብ ጽንፈኞችን በማጋለጥ ለህግ የበላይነት መረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚጠበቅበትም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025