
ባህር ዳር፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የባህርዳር ከተማን ሰላም ለመጠበቅና የተረጋጋ ግብይት እንዲኖር ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ የከተማዋ ነጋዴዎች ተናገሩ።
"የጥፋት እጆቹና መዘዞቹ " በሚል መሪ ሃሳብ ከባህር ዳር ከተማ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ጋር ዛሬ የውይይት መድረክ ተካሄዷል።
የውይይቱ ተሳታፊ ነጋዴ ወይዘሮ ዘነበች መንግስቴ፤ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።
ይህም በሸማቹ ህብረተሰብ ላይ ችግር እየፈጠረ እንደሚገኝ ጠቁመው፥ መፍትሄ ለመሻት እየተደረገ ባለው ጥረት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡም ተናግረዋል።
ሌላኛዋ የሸቀጣ ሸቀጥ ነጋዴ ወጣት ምሳነሽ እናናው፤ የጽንፈኝነት አስተሳሰብን መከላከል የንግዱ ማህበረሰብን ጨምሮ የሁሉም ህብረተሰብ ኃላፊነት መሆን እንዳለበት ገልጻለች።
በዚህም የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ራስን መፈተሽና ከጽንፈኝነት አስተሳሰብ ከማውጣት በዘለለ በተሳሳተ መንገድ ውስጥ ያሉ ወገኖችን መምከር ይጠበቅበታል ብለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የባህር ዳር ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ብርሃን ንጉሴ በሰጡት ማብራሪያ፥ የጽንፈኝነት አስተሳሰብ የወለደው የሰላም እጦት በክልሉ ተጽእኖ አሳድሯል።
ይህም የንግዱ ማህበረሰብ ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ ስራውን እንደልቡ እንዳይሰራና ተረጋግቶ እንዳይኖር በማድረጉ በሸማቹ ላይም ተጽእኖው እንዲኖር አድርጓል ብለዋል።
የንግዱ ማህበረሰብም መንግስት ችግሩን በውይይትና በንግግር ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት ማገዝና መደገፍ ይጠበቅበታል ብለዋል።
በተጨማሪም የንግዱ ማህበረሰብ ጽንፈኞችን በማጋለጥ ለህግ የበላይነት መረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚጠበቅበትም አሳስበዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025