ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ9 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ አጸደ አይዛ እንደገለጹት፤ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጠው ለ151 ባለሀብቶች ነው።
ባለሃበቶቹ ፈቃዱ የተሰጣቸው በግብርና፣አገልግሎትና ኢንዱስትሪ ዘርፎች ለመሰማራት ጠይቀው መሆኑን ጠቅሰው፤ ከ33 ሺህ ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩ የሚጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን ላይ 90 ሺህ 575 ሄክታር መሬት ተለይቶ መቀመጡን ጠቅሰው፤ እየመጡ ያሉ በርካታ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ጥያቄዎች አዋጪነታቸው እየታየ እንደሚስተናገድ አስረድተዋል።
ከዚህ ሌላ የተሰጣቸውን መሬት ሳያለሙ አጥረው ያስቀምጡና ላልተገባ ስራ ሲጠቀሙ የተገኙ 34 ባለሀብቶች ውላቸው መቋረጡን ጠቁመው፤ ለ62 ደግሞ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል።
ክልሉ ሰፊ ጸጋ እንዳለው አመልክተው፤ ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ 350 ባለሀብቶች ፈቃድ ወስደው ስራ ላይ መሆናቸውን አንስተዋል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ፍሬው ሞገስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥በአካባቢው የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እየተነቃቃ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ በተቀናጀ መንገድ የመደገፍና ክትትል ስራ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተው፤ በገቡት ውል መሰረት ወደስራ ያልገቡትን ህጋዊ እርምጃ የመውሰድ ስራ መጠናከሩን ተናግረዋል።
በከተማው የአንጂዲ ዱቄት ፋብሪካ ባለቤት ወይዘሮ ፀጋነሽ ወልደጊዮርጊስ ፤በመንግስት በኩል የሚደረግ ድጋፍና ክትትል የሚያበረታታ መሆኑን አንስተው፤ አሁን ላይ ድርጅታቸው ከ100 ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመዋል።
በቀጣይም ከዚህ በላይ አስፍተው ለመስራት የማስፋፊያ ቦታ ጠይቀው እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
የፖስታ እና ማካሮኒ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እየገነቡ ያሉት አቶ እንዳለ ጎአ በበኩላቸው፥ በመንግስት በኩል እየተደረገ ያለው ድጋፍ መልካም መሆኑን ገልጸዋል።
ግንባታው ሲያልቅ ለ200 ዜጎች የስራ ዕድል ይፈጥራልም ነው ያሉት።
የክልሉ የስራ ሃላፊዎች በወላይታ ሶዶ ከተማ የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ዛሬ ተመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025