የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ9 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ

May 19, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ9 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።


የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ አጸደ አይዛ እንደገለጹት፤ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጠው ለ151 ባለሀብቶች ነው።


ባለሃበቶቹ ፈቃዱ የተሰጣቸው በግብርና፣አገልግሎትና ኢንዱስትሪ ዘርፎች ለመሰማራት ጠይቀው መሆኑን ጠቅሰው፤ ከ33 ሺህ ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩ የሚጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል።


አሁን ላይ 90 ሺህ 575 ሄክታር መሬት ተለይቶ መቀመጡን ጠቅሰው፤ እየመጡ ያሉ በርካታ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ጥያቄዎች አዋጪነታቸው እየታየ እንደሚስተናገድ አስረድተዋል።


ከዚህ ሌላ የተሰጣቸውን መሬት ሳያለሙ አጥረው ያስቀምጡና ላልተገባ ስራ ሲጠቀሙ የተገኙ 34 ባለሀብቶች ውላቸው መቋረጡን ጠቁመው፤ ለ62 ደግሞ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል።


ክልሉ ሰፊ ጸጋ እንዳለው አመልክተው፤ ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ 350 ባለሀብቶች ፈቃድ ወስደው ስራ ላይ መሆናቸውን አንስተዋል።


የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ፍሬው ሞገስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥በአካባቢው የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እየተነቃቃ መሆኑን ገልጸዋል።


የኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ በተቀናጀ መንገድ የመደገፍና ክትትል ስራ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተው፤ በገቡት ውል መሰረት ወደስራ ያልገቡትን ህጋዊ እርምጃ የመውሰድ ስራ መጠናከሩን ተናግረዋል።


በከተማው የአንጂዲ ዱቄት ፋብሪካ ባለቤት ወይዘሮ ፀጋነሽ ወልደጊዮርጊስ ፤በመንግስት በኩል የሚደረግ ድጋፍና ክትትል የሚያበረታታ መሆኑን አንስተው፤ አሁን ላይ ድርጅታቸው ከ100 ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመዋል።


በቀጣይም ከዚህ በላይ አስፍተው ለመስራት የማስፋፊያ ቦታ ጠይቀው እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


የፖስታ እና ማካሮኒ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እየገነቡ ያሉት አቶ እንዳለ ጎአ በበኩላቸው፥ በመንግስት በኩል እየተደረገ ያለው ድጋፍ መልካም መሆኑን ገልጸዋል።


ግንባታው ሲያልቅ ለ200 ዜጎች የስራ ዕድል ይፈጥራልም ነው ያሉት።


የክልሉ የስራ ሃላፊዎች በወላይታ ሶዶ ከተማ የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ዛሬ ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025