
ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ9 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ አጸደ አይዛ እንደገለጹት፤ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጠው ለ151 ባለሀብቶች ነው።
ባለሃበቶቹ ፈቃዱ የተሰጣቸው በግብርና፣አገልግሎትና ኢንዱስትሪ ዘርፎች ለመሰማራት ጠይቀው መሆኑን ጠቅሰው፤ ከ33 ሺህ ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩ የሚጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን ላይ 90 ሺህ 575 ሄክታር መሬት ተለይቶ መቀመጡን ጠቅሰው፤ እየመጡ ያሉ በርካታ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ጥያቄዎች አዋጪነታቸው እየታየ እንደሚስተናገድ አስረድተዋል።
ከዚህ ሌላ የተሰጣቸውን መሬት ሳያለሙ አጥረው ያስቀምጡና ላልተገባ ስራ ሲጠቀሙ የተገኙ 34 ባለሀብቶች ውላቸው መቋረጡን ጠቁመው፤ ለ62 ደግሞ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል።
ክልሉ ሰፊ ጸጋ እንዳለው አመልክተው፤ ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ 350 ባለሀብቶች ፈቃድ ወስደው ስራ ላይ መሆናቸውን አንስተዋል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ፍሬው ሞገስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥በአካባቢው የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እየተነቃቃ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ በተቀናጀ መንገድ የመደገፍና ክትትል ስራ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተው፤ በገቡት ውል መሰረት ወደስራ ያልገቡትን ህጋዊ እርምጃ የመውሰድ ስራ መጠናከሩን ተናግረዋል።
በከተማው የአንጂዲ ዱቄት ፋብሪካ ባለቤት ወይዘሮ ፀጋነሽ ወልደጊዮርጊስ ፤በመንግስት በኩል የሚደረግ ድጋፍና ክትትል የሚያበረታታ መሆኑን አንስተው፤ አሁን ላይ ድርጅታቸው ከ100 ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመዋል።
በቀጣይም ከዚህ በላይ አስፍተው ለመስራት የማስፋፊያ ቦታ ጠይቀው እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
የፖስታ እና ማካሮኒ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እየገነቡ ያሉት አቶ እንዳለ ጎአ በበኩላቸው፥ በመንግስት በኩል እየተደረገ ያለው ድጋፍ መልካም መሆኑን ገልጸዋል።
ግንባታው ሲያልቅ ለ200 ዜጎች የስራ ዕድል ይፈጥራልም ነው ያሉት።
የክልሉ የስራ ሃላፊዎች በወላይታ ሶዶ ከተማ የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ዛሬ ተመልክተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025