የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ9 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ

May 19, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ9 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።


የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ አጸደ አይዛ እንደገለጹት፤ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጠው ለ151 ባለሀብቶች ነው።


ባለሃበቶቹ ፈቃዱ የተሰጣቸው በግብርና፣አገልግሎትና ኢንዱስትሪ ዘርፎች ለመሰማራት ጠይቀው መሆኑን ጠቅሰው፤ ከ33 ሺህ ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩ የሚጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል።


አሁን ላይ 90 ሺህ 575 ሄክታር መሬት ተለይቶ መቀመጡን ጠቅሰው፤ እየመጡ ያሉ በርካታ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ጥያቄዎች አዋጪነታቸው እየታየ እንደሚስተናገድ አስረድተዋል።


ከዚህ ሌላ የተሰጣቸውን መሬት ሳያለሙ አጥረው ያስቀምጡና ላልተገባ ስራ ሲጠቀሙ የተገኙ 34 ባለሀብቶች ውላቸው መቋረጡን ጠቁመው፤ ለ62 ደግሞ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል።


ክልሉ ሰፊ ጸጋ እንዳለው አመልክተው፤ ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ 350 ባለሀብቶች ፈቃድ ወስደው ስራ ላይ መሆናቸውን አንስተዋል።


የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ፍሬው ሞገስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥በአካባቢው የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እየተነቃቃ መሆኑን ገልጸዋል።


የኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ በተቀናጀ መንገድ የመደገፍና ክትትል ስራ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተው፤ በገቡት ውል መሰረት ወደስራ ያልገቡትን ህጋዊ እርምጃ የመውሰድ ስራ መጠናከሩን ተናግረዋል።


በከተማው የአንጂዲ ዱቄት ፋብሪካ ባለቤት ወይዘሮ ፀጋነሽ ወልደጊዮርጊስ ፤በመንግስት በኩል የሚደረግ ድጋፍና ክትትል የሚያበረታታ መሆኑን አንስተው፤ አሁን ላይ ድርጅታቸው ከ100 ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመዋል።


በቀጣይም ከዚህ በላይ አስፍተው ለመስራት የማስፋፊያ ቦታ ጠይቀው እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


የፖስታ እና ማካሮኒ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እየገነቡ ያሉት አቶ እንዳለ ጎአ በበኩላቸው፥ በመንግስት በኩል እየተደረገ ያለው ድጋፍ መልካም መሆኑን ገልጸዋል።


ግንባታው ሲያልቅ ለ200 ዜጎች የስራ ዕድል ይፈጥራልም ነው ያሉት።


የክልሉ የስራ ሃላፊዎች በወላይታ ሶዶ ከተማ የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ዛሬ ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026