አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2017(ኢዜአ)፡- ኤምብሬር የአውሮፕላን አምራች ኩባንያ በኢትዮጵያ በአቪዬሽን ኢንቨስትመንት መሰማራት እንደሚሻ አስታወቀ።
የኩባንያው የአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ ተቋማዊ ግንኙነት ዋና ስራ አስኪያጅ ሁሴን ዳባስ ኢትዮጵያ የህግ ማዕቀፎችን፣ የኢንቨስትመንት ስነ-ምህዳርና አሰራሮችን በማሻሻል የውጭ ባለሀብቶችን እየሳበች እንደምትገኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል።
የመንግስት እርምጃ እና አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በመሳብ ከቀዳሚዎቹ ስፍራ እንድትቀመጥ ማድረጉን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ዘርፍ ያደነቁ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ግዙፉ እና በዓለም ላይ ከሚገኙ ትላልቅ አየር መንገዶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው ብለዋል።
በትራንስፖርት ዘርፍ የታየውን እድገትም አስገራሚ ሲሉ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ሁሉም ዘርፎች ለባለሀብቶች ሳቢ ናቸው ያሉት ስራ አስኪያጁ የትራንስፖርት ዘርፉ በተለይ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ የሚያስችል ሁኔታ አለው ነው ያሉት።
በዚህ ረገድም የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካርጎ አገልግሎት አሰጣጥ፣ የጥገና መስጫዎች፣ የማሰልጠኛ ማዕከላት እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ኤምብሬር ኩባንያ የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንትና የእድገት አካል መሆን እንደሚፈልግ ጠቅሰው በአቪዬሽን ኢንቨስትመንት በተለያዩ ዘርፎች የመሰማራት ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ተናግረዋል።
ኩባንያው ለመንገደኞችም ሆነ ለጭነት አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ዓይነት አውሮፕላኖችን ያመርታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025