
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2017(ኢዜአ)፡- ኤምብሬር የአውሮፕላን አምራች ኩባንያ በኢትዮጵያ በአቪዬሽን ኢንቨስትመንት መሰማራት እንደሚሻ አስታወቀ።
የኩባንያው የአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ ተቋማዊ ግንኙነት ዋና ስራ አስኪያጅ ሁሴን ዳባስ ኢትዮጵያ የህግ ማዕቀፎችን፣ የኢንቨስትመንት ስነ-ምህዳርና አሰራሮችን በማሻሻል የውጭ ባለሀብቶችን እየሳበች እንደምትገኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል።
የመንግስት እርምጃ እና አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በመሳብ ከቀዳሚዎቹ ስፍራ እንድትቀመጥ ማድረጉን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ዘርፍ ያደነቁ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ግዙፉ እና በዓለም ላይ ከሚገኙ ትላልቅ አየር መንገዶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው ብለዋል።
በትራንስፖርት ዘርፍ የታየውን እድገትም አስገራሚ ሲሉ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ሁሉም ዘርፎች ለባለሀብቶች ሳቢ ናቸው ያሉት ስራ አስኪያጁ የትራንስፖርት ዘርፉ በተለይ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ የሚያስችል ሁኔታ አለው ነው ያሉት።
በዚህ ረገድም የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካርጎ አገልግሎት አሰጣጥ፣ የጥገና መስጫዎች፣ የማሰልጠኛ ማዕከላት እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ኤምብሬር ኩባንያ የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንትና የእድገት አካል መሆን እንደሚፈልግ ጠቅሰው በአቪዬሽን ኢንቨስትመንት በተለያዩ ዘርፎች የመሰማራት ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ተናግረዋል።
ኩባንያው ለመንገደኞችም ሆነ ለጭነት አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ዓይነት አውሮፕላኖችን ያመርታል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026