
አዲስ አበባ ፤ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦የሥራ ስምሪት መርሃ ግብሮችን ከአገራዊ ልማት ጋር በማጣጣም ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ።
20ኛው የዓለም ሥራ ድርጅት በሥራ ላይ የተመሰረተ የባለሙያዎች አህጉራዊ ስብሰባ "የማይበገር ማህበረሰብ እና ጤናማ አካባቢ የሰው ኃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም አካሄዶች" በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።
በስብሰባው የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት ተወካዮች፣የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።
የጉባኤው ተሳታፊ የሆኑ 25 የአፍሪካ ሀገራት ምቹ የስራ ምህዳር ለመፍጠር የሚያስችል የጋራ አቋም መግለጫ አውጥተዋል።
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ የጋራ አቋም መግለጫውን በንባብ ያሰሙ ሲሆን፤የተጠናከረ የሥራ ልማት ቅጥር ፕሮግራም አካሄድ በተገቢው ስትራቴጂ መምራት እንደሚገባ አንስተዋል።
የሥራ ስምሪት መርሃ ግብሮች ከአገራዊ ልማት ጋር በማጣጣም ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ በአቋም መግለጫው ተመላክቷል።
የፖሊሲ ወጥነትን ማሳደግ እና በተለያዩ የአፈፃፀም እና የአስተዳደር መዋቅሮች መካከል ያለውን ትብብር ማሻሻል እንደሚያስፈልግም ተገልጿል።
የሥራ ገበያን የመተንተን አቅምን ማሳደግ እንደሚገባ እና የፋይናንስ ተቋማት የኢንቨስትመንት ውሳኔዎችን በመደገፍና በማጠናከር የተፈጠሩ የስራ ስምሪቶችን በተሻለ መንገድ ለመከታተል እንደሚያስችል ተጠቁሟል።
በጋራ አቋም መግለጫ የተቀመጡ ተግባራት አፈፃፀም ሂደትን ለመከታተል ተገቢ የሆነ የክትትል እና የግምገማ ስርዓቶች እና መረጃን መሰብሰብ እና መለዋወጥ እንደሚገባም ተመላክቷል።
የአለም አቀፍ የስራ ድርጅት ሀገራት ይህን የጋራ መግለጫ ገቢራዊ ለማድረግ ለሚጠይቁት ድጋፍ የበኩሉን እንዲወጣ በአቋም መግለጫው ጥሪ ቀርቧል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026