የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የሥራ ስምሪት መርሃ ግብሮችን ከአገራዊ ልማት ጋር በማጣጣም ተግባራዊ ማድረግ ይገባል

May 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦የሥራ ስምሪት መርሃ ግብሮችን ከአገራዊ ልማት ጋር በማጣጣም ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ።

20ኛው የዓለም ሥራ ድርጅት በሥራ ላይ የተመሰረተ የባለሙያዎች አህጉራዊ ስብሰባ "የማይበገር ማህበረሰብ እና ጤናማ አካባቢ የሰው ኃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም አካሄዶች" በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

በስብሰባው የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት ተወካዮች፣የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።

የጉባኤው ተሳታፊ የሆኑ 25 የአፍሪካ ሀገራት ምቹ የስራ ምህዳር ለመፍጠር የሚያስችል የጋራ አቋም መግለጫ አውጥተዋል።

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ የጋራ አቋም መግለጫውን በንባብ ያሰሙ ሲሆን፤የተጠናከረ የሥራ ልማት ቅጥር ፕሮግራም አካሄድ በተገቢው ስትራቴጂ መምራት እንደሚገባ አንስተዋል።

የሥራ ስምሪት መርሃ ግብሮች ከአገራዊ ልማት ጋር በማጣጣም ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ በአቋም መግለጫው ተመላክቷል።

የፖሊሲ ወጥነትን ማሳደግ እና በተለያዩ የአፈፃፀም እና የአስተዳደር መዋቅሮች መካከል ያለውን ትብብር ማሻሻል እንደሚያስፈልግም ተገልጿል።

‎የሥራ ገበያን የመተንተን አቅምን ማሳደግ እንደሚገባ እና የፋይናንስ ተቋማት የኢንቨስትመንት ውሳኔዎችን በመደገፍና በማጠናከር የተፈጠሩ የስራ ስምሪቶችን በተሻለ መንገድ ለመከታተል እንደሚያስችል ተጠቁሟል።

በጋራ አቋም መግለጫ የተቀመጡ ተግባራት አፈፃፀም ሂደትን ለመከታተል ተገቢ የሆነ የክትትል እና የግምገማ ስርዓቶች እና መረጃን መሰብሰብ እና መለዋወጥ እንደሚገባም ተመላክቷል።

የአለም አቀፍ የስራ ድርጅት ሀገራት ይህን የጋራ መግለጫ ገቢራዊ ለማድረግ ለሚጠይቁት ድጋፍ የበኩሉን እንዲወጣ በአቋም መግለጫው ጥሪ ቀርቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025