
አዲስ አበባ ፤ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦የሥራ ስምሪት መርሃ ግብሮችን ከአገራዊ ልማት ጋር በማጣጣም ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ።
20ኛው የዓለም ሥራ ድርጅት በሥራ ላይ የተመሰረተ የባለሙያዎች አህጉራዊ ስብሰባ "የማይበገር ማህበረሰብ እና ጤናማ አካባቢ የሰው ኃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም አካሄዶች" በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።
በስብሰባው የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት ተወካዮች፣የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።
የጉባኤው ተሳታፊ የሆኑ 25 የአፍሪካ ሀገራት ምቹ የስራ ምህዳር ለመፍጠር የሚያስችል የጋራ አቋም መግለጫ አውጥተዋል።
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ የጋራ አቋም መግለጫውን በንባብ ያሰሙ ሲሆን፤የተጠናከረ የሥራ ልማት ቅጥር ፕሮግራም አካሄድ በተገቢው ስትራቴጂ መምራት እንደሚገባ አንስተዋል።
የሥራ ስምሪት መርሃ ግብሮች ከአገራዊ ልማት ጋር በማጣጣም ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ በአቋም መግለጫው ተመላክቷል።
የፖሊሲ ወጥነትን ማሳደግ እና በተለያዩ የአፈፃፀም እና የአስተዳደር መዋቅሮች መካከል ያለውን ትብብር ማሻሻል እንደሚያስፈልግም ተገልጿል።
የሥራ ገበያን የመተንተን አቅምን ማሳደግ እንደሚገባ እና የፋይናንስ ተቋማት የኢንቨስትመንት ውሳኔዎችን በመደገፍና በማጠናከር የተፈጠሩ የስራ ስምሪቶችን በተሻለ መንገድ ለመከታተል እንደሚያስችል ተጠቁሟል።
በጋራ አቋም መግለጫ የተቀመጡ ተግባራት አፈፃፀም ሂደትን ለመከታተል ተገቢ የሆነ የክትትል እና የግምገማ ስርዓቶች እና መረጃን መሰብሰብ እና መለዋወጥ እንደሚገባም ተመላክቷል።
የአለም አቀፍ የስራ ድርጅት ሀገራት ይህን የጋራ መግለጫ ገቢራዊ ለማድረግ ለሚጠይቁት ድጋፍ የበኩሉን እንዲወጣ በአቋም መግለጫው ጥሪ ቀርቧል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025