
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመተግበር ዘመናዊና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበች መሆኑን የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 ላይ የተሳተፉ የውጭ ኩባንያዎች ገለጹ።
ከፈጣኑንና ተለዋዋጩ የአለም ነባራዊ ሁኔታ እኩል ለመራመድ የዲጂታል ስነ-ምህዳር መፍጠርና የዲጂታል ክህሎትን ማጎልበት ለነገ የማይባል ሥራ መሆኑ በተደጋጋሚ ይጠቀሳል።
ከፍተኛ የወጣት ቁጥር ባላት ኢትዮጵያም በዲጂታል ቴክኖሎጂ የወጣቱን አምቅ አቅም ተጠቅማ ልማቷን ለማፋጠን የተለያዩ ስራዎች እያከናወነች ትገኛለች።
መንግሥት የቴክኖሎጂ ፈጠራን የሚደግፉ ፖሊሲና ሰትራቴጂዎችን ከመቅረጽ ባለፈ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከላትን እያሰፋ ይገኛል።
ከቀናት በፊት በተካሄደው የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች እየተገበረቻቸው ያሉ ቴክኖሎጂዎችን ለአለም ለማስተዋወቅ ያስቻለ ነው።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በስታርታፕና በተለያዩ የፈጠራ ውጤቶች ቴክኖሎጂን በመጠቀም ምርትና አገልግሎትን ማቀላጠፍና ማስፋት መቻሉን ኤክስፖው በተግባር አሳይቷል።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡና በኤክስፖው የተሳተፉ የተለያዩ ሀገራት ኩባንያዎችም የኢትዮጵያን ፈጣን የቴክኖሎጂ ዕድገት አድንቀዋል።
የቴክኖሎጂ ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የቴክኖሎጂ ሥነ-ምህዳር በመጠቀም ከተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት ጋር እየሰሩ መሆኑን አመልክተዋል።

የቻይና ኩባንያ የሆነው ኒውታክ ሽያጭ ማናጀር ሶፒ ዛኦ ኩባንያው የተለያዩ ጭነቶችን በስካነር የፍተሻ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ኩባንያው ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በመሆን በተለያዩ ድንበሮች ላይ ኮንቴነሮችን በስካነር የመፈተሽ ስራ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
እንዲ አይነት ቴክኖሎጂዎች የሀገራትን ስማርት ሲቲ ግንባታ እንደሚያፋጥኑና አገልግሎታቸውን ፈጣንና ዘመናዊ ለማድረግ ወሳኝ መሆናቸውንም አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ በማድረግ ስማርት ሲቲ ለመገንባትና አገልግሎቶችን ለማዘመን እያደረገችው ያለውን ጥረትም አድንቀዋል።

ወተር ፎል የተባለው አለም አቀፍ ኩባንያ ሽያጭ ማናጀር ናደር ባዳዲ በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ በርካታ ወጣቶች ያላቸውን የቴክኖሎጂና የፈጠራ አቅም በቀላሉ መረዳት ችያለሁ ብለዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሀገሪቱ በብዙ ዘርፎች ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበች መሆኑን አንስተው ለዚህ ደግሞ የቴክኖሎጂ ተደራሽነትን ለማስፋት ያደረገችው ጥረት ተጠቃሚ አድርጓታል ነው ያሉት።
የቻይና ኩባንያ የሆነው ኒውታክ ሽያጭ ማናጀር ሶፒ ዛኦ በኢትዮጵያ የረጅም ዓመት የስራ ቆይታ ማድረጋቸውን አስታውሰው በየጊዜው እየታየ ያለውን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዕድገት አድንቀዋል።

የክላውድ ኮምፒዩተርና ዳታ አገልግሎት የሽያጭ ዳይሬክተር ሊዊስ ሊዮ ኩባንያቸው ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በሲም ካርድ አስተዳደር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ደግሞ በተማሪዎች መረጃ አያያዝ ሲስተም ላይ በጋራ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ የተለያዩ አገልግሎቶችን በዲጂታል በመታገዝ ለመስጠት የምታደርገው ጥረት የዜጎችን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ አገልግሎቶቸን ያቀላጥፋል ብለዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026