የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ምሁራን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ ማፍራትን አጠናክረው ማስቀጠል ይጠበቅባቸዋል - ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር)

May 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2017(ኢዜአ)፦ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቅ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ የማፍራት ስራን አጠናክረው ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ገለጹ።

''ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል፤ ሀገር በትምህርት ይበለጽጋል'' በሚል መሪ ሃሳብ ሀገራዊ ለውጡ በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶችንና የቀጣይ ሀገራዊ ትኩረት መስኮችን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ውይይት ተካሂዷል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ስኬት ማስመዝገብ ተችሏል።


በዩኒቨርሲቲው የውይይቱ ተሳታፊ ምሁራን የሚቀርቡ ሃሳቦችም በቀጣይ የልማት አቅጣጫዎች ላይ በግብዓትነት እንደሚውሉ አስታውቀዋል።

ይህም ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ለምትገኘው ለውጥም የምሁራን ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በዚህም በምዕራፍ አንድና ሁለት ተግባራዊ የተደረገው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም የማክሮ አመላካቾች ስኬት ማስመዝገብ እንደተቻለ አስረድተዋል።

በማህበራዊና የኢኮኖሚ የልማት ስራዎች እንዲሁም በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት ያማከሉ ስኬታማ ስራዎች ውይይት እንደተደረገባቸም ጠቅሰዋል።

በውይይቱ ምሁራን ለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች መፍትሄ አመላካች የጥናትና ምርምር ስራን ማጠናከርና ለፖሊሲ ግብዓት እንዲውሉ ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው ብለዋል።

በቀጣይም ምሁራን በዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ፣ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ በማፍራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቅ ዜጋ ማፍራት ላይ ይበልጥ ማተኮር እንዳለባቸው ነው የገለጹት።

ሀገር ወዳድ፣ ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በማጎልበት ዴሞክራሲያዊ ዜጋን የማፍራት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸውም አስረድተዋል።


የውይይቱ ተሳታፊ ምሁራንም በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና ዲፕሎማሲ ተግባራዊ የማሻሻያ እርምጃዎች ለሀገር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማዋል እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

በቡና የወጪ ንግድ ምርት መጠንን በመጨመር በኩል የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው፣ እሴትን ጨምሮ ለገበያ መላክ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል።


ከተሞችን አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ከማድረግ አንጻር ያለው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም አዲስ አበባ ከተማን በኮሪደር ልማት በማስዋብ የተሰራው ስራ ትልቅ ለውጥ መሆኑን ምሁራኑ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025