የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ምሁራን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ ማፍራትን አጠናክረው ማስቀጠል ይጠበቅባቸዋል - ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር)

May 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2017(ኢዜአ)፦ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቅ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ የማፍራት ስራን አጠናክረው ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ገለጹ።

''ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል፤ ሀገር በትምህርት ይበለጽጋል'' በሚል መሪ ሃሳብ ሀገራዊ ለውጡ በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶችንና የቀጣይ ሀገራዊ ትኩረት መስኮችን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ውይይት ተካሂዷል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ስኬት ማስመዝገብ ተችሏል።


በዩኒቨርሲቲው የውይይቱ ተሳታፊ ምሁራን የሚቀርቡ ሃሳቦችም በቀጣይ የልማት አቅጣጫዎች ላይ በግብዓትነት እንደሚውሉ አስታውቀዋል።

ይህም ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ለምትገኘው ለውጥም የምሁራን ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በዚህም በምዕራፍ አንድና ሁለት ተግባራዊ የተደረገው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም የማክሮ አመላካቾች ስኬት ማስመዝገብ እንደተቻለ አስረድተዋል።

በማህበራዊና የኢኮኖሚ የልማት ስራዎች እንዲሁም በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት ያማከሉ ስኬታማ ስራዎች ውይይት እንደተደረገባቸም ጠቅሰዋል።

በውይይቱ ምሁራን ለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች መፍትሄ አመላካች የጥናትና ምርምር ስራን ማጠናከርና ለፖሊሲ ግብዓት እንዲውሉ ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው ብለዋል።

በቀጣይም ምሁራን በዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ፣ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ በማፍራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቅ ዜጋ ማፍራት ላይ ይበልጥ ማተኮር እንዳለባቸው ነው የገለጹት።

ሀገር ወዳድ፣ ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በማጎልበት ዴሞክራሲያዊ ዜጋን የማፍራት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸውም አስረድተዋል።


የውይይቱ ተሳታፊ ምሁራንም በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና ዲፕሎማሲ ተግባራዊ የማሻሻያ እርምጃዎች ለሀገር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማዋል እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

በቡና የወጪ ንግድ ምርት መጠንን በመጨመር በኩል የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው፣ እሴትን ጨምሮ ለገበያ መላክ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል።


ከተሞችን አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ከማድረግ አንጻር ያለው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም አዲስ አበባ ከተማን በኮሪደር ልማት በማስዋብ የተሰራው ስራ ትልቅ ለውጥ መሆኑን ምሁራኑ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026