የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ምሁራን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ ማፍራትን አጠናክረው ማስቀጠል ይጠበቅባቸዋል - ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር)

May 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2017(ኢዜአ)፦ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቅ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ የማፍራት ስራን አጠናክረው ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ገለጹ።

''ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል፤ ሀገር በትምህርት ይበለጽጋል'' በሚል መሪ ሃሳብ ሀገራዊ ለውጡ በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶችንና የቀጣይ ሀገራዊ ትኩረት መስኮችን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ውይይት ተካሂዷል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ስኬት ማስመዝገብ ተችሏል።


በዩኒቨርሲቲው የውይይቱ ተሳታፊ ምሁራን የሚቀርቡ ሃሳቦችም በቀጣይ የልማት አቅጣጫዎች ላይ በግብዓትነት እንደሚውሉ አስታውቀዋል።

ይህም ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ለምትገኘው ለውጥም የምሁራን ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በዚህም በምዕራፍ አንድና ሁለት ተግባራዊ የተደረገው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም የማክሮ አመላካቾች ስኬት ማስመዝገብ እንደተቻለ አስረድተዋል።

በማህበራዊና የኢኮኖሚ የልማት ስራዎች እንዲሁም በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት ያማከሉ ስኬታማ ስራዎች ውይይት እንደተደረገባቸም ጠቅሰዋል።

በውይይቱ ምሁራን ለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች መፍትሄ አመላካች የጥናትና ምርምር ስራን ማጠናከርና ለፖሊሲ ግብዓት እንዲውሉ ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው ብለዋል።

በቀጣይም ምሁራን በዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ፣ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ በማፍራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቅ ዜጋ ማፍራት ላይ ይበልጥ ማተኮር እንዳለባቸው ነው የገለጹት።

ሀገር ወዳድ፣ ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በማጎልበት ዴሞክራሲያዊ ዜጋን የማፍራት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸውም አስረድተዋል።


የውይይቱ ተሳታፊ ምሁራንም በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና ዲፕሎማሲ ተግባራዊ የማሻሻያ እርምጃዎች ለሀገር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማዋል እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

በቡና የወጪ ንግድ ምርት መጠንን በመጨመር በኩል የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው፣ እሴትን ጨምሮ ለገበያ መላክ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል።


ከተሞችን አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ከማድረግ አንጻር ያለው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም አዲስ አበባ ከተማን በኮሪደር ልማት በማስዋብ የተሰራው ስራ ትልቅ ለውጥ መሆኑን ምሁራኑ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025