አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2017(ኢዜአ)፦ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቅ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ የማፍራት ስራን አጠናክረው ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ገለጹ።
''ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል፤ ሀገር በትምህርት ይበለጽጋል'' በሚል መሪ ሃሳብ ሀገራዊ ለውጡ በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶችንና የቀጣይ ሀገራዊ ትኩረት መስኮችን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ውይይት ተካሂዷል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ስኬት ማስመዝገብ ተችሏል።
በዩኒቨርሲቲው የውይይቱ ተሳታፊ ምሁራን የሚቀርቡ ሃሳቦችም በቀጣይ የልማት አቅጣጫዎች ላይ በግብዓትነት እንደሚውሉ አስታውቀዋል።
ይህም ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ለምትገኘው ለውጥም የምሁራን ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በዚህም በምዕራፍ አንድና ሁለት ተግባራዊ የተደረገው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም የማክሮ አመላካቾች ስኬት ማስመዝገብ እንደተቻለ አስረድተዋል።
በማህበራዊና የኢኮኖሚ የልማት ስራዎች እንዲሁም በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት ያማከሉ ስኬታማ ስራዎች ውይይት እንደተደረገባቸም ጠቅሰዋል።
በውይይቱ ምሁራን ለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች መፍትሄ አመላካች የጥናትና ምርምር ስራን ማጠናከርና ለፖሊሲ ግብዓት እንዲውሉ ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው ብለዋል።
በቀጣይም ምሁራን በዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ፣ በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ በማፍራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቅ ዜጋ ማፍራት ላይ ይበልጥ ማተኮር እንዳለባቸው ነው የገለጹት።
ሀገር ወዳድ፣ ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በማጎልበት ዴሞክራሲያዊ ዜጋን የማፍራት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸውም አስረድተዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ ምሁራንም በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና ዲፕሎማሲ ተግባራዊ የማሻሻያ እርምጃዎች ለሀገር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማዋል እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።
በቡና የወጪ ንግድ ምርት መጠንን በመጨመር በኩል የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው፣ እሴትን ጨምሮ ለገበያ መላክ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል።
ከተሞችን አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ከማድረግ አንጻር ያለው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም አዲስ አበባ ከተማን በኮሪደር ልማት በማስዋብ የተሰራው ስራ ትልቅ ለውጥ መሆኑን ምሁራኑ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025