የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በሀገር አቀፍ ደረጃ 24 የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች በዚህ ሳምንት በይፋ ስራ ይጀምራሉ

May 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 18/2017(ኢዜአ)፦በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ክልሎች እና በአስር የፌደራል ተቋማት የተገነቡ 24 የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች በዚህ ሳምንት በይፋ ስራ እንደሚጀምሩ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ከዚህ ቀደም በ5 ተቋማት የተገነቡ ስማርት ክፍሎች አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸውንም ገልጿል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽሩን አለማየሁ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎቹ የተለያዩ ቦታ ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትን በቀላሉ እንዲገናኙና ስራቸውን እንዲያሳልጡ የሚያስችሉ ናቸው።

ልዩ ልዩ ስራዎችን፣ስብሰባዎችንና ስልጠናዎችን ጊዜና ወጪን ቆጣቢ በሆነ መንገድ በቀላሉ መምራት የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እንደተዘረጋላቸው አመልክተዋል።

ስማርት ስክሪን፣ ስማርት ላይቲንግ፣ የተሻሻሉ የቴሌ እና የቪዲዮ ኮንፈረንሶችን ማድረግ የሚያስችሉ የኔትወርክ፣ የድምፅ ብክለትን የሚቀንሱ(Soundproofing) መሳሪያዎች ተገጥሞላቸዋል ነው ያሉት።

በሀገርአቀፍ ደረጃ 24ቱ የስማርት የኮሙኒኬሽን ክፍሎች ከነገ በስቲያ በተመሳሳይ ሰዓት ተመርቀው በይፋ ስራ እንደሚጀምሩም ገልጸዋል።

በሁሉም ክልሎች፣በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በተመረጡ አስር የፌዴራል ተቋማት የተገነቡት እነዚህ ስማርት የኮሙኒኬሽን ክፍሎች ግንባታ አንድ ዓመት መውሰዱንም ነው የገለጹት።

ቀጣይነት ያለው አገልግሎት እንዲሰጡም ለባለሙያዎች የአጠቃቀም ማንዋልና የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎቹን በሁሉም ተቋማት ለማዳረስ ከክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ጋር እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025