የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በሀገር አቀፍ ደረጃ 24 የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች በዚህ ሳምንት በይፋ ስራ ይጀምራሉ

May 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 18/2017(ኢዜአ)፦በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ክልሎች እና በአስር የፌደራል ተቋማት የተገነቡ 24 የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች በዚህ ሳምንት በይፋ ስራ እንደሚጀምሩ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ከዚህ ቀደም በ5 ተቋማት የተገነቡ ስማርት ክፍሎች አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸውንም ገልጿል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽሩን አለማየሁ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎቹ የተለያዩ ቦታ ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትን በቀላሉ እንዲገናኙና ስራቸውን እንዲያሳልጡ የሚያስችሉ ናቸው።

ልዩ ልዩ ስራዎችን፣ስብሰባዎችንና ስልጠናዎችን ጊዜና ወጪን ቆጣቢ በሆነ መንገድ በቀላሉ መምራት የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እንደተዘረጋላቸው አመልክተዋል።

ስማርት ስክሪን፣ ስማርት ላይቲንግ፣ የተሻሻሉ የቴሌ እና የቪዲዮ ኮንፈረንሶችን ማድረግ የሚያስችሉ የኔትወርክ፣ የድምፅ ብክለትን የሚቀንሱ(Soundproofing) መሳሪያዎች ተገጥሞላቸዋል ነው ያሉት።

በሀገርአቀፍ ደረጃ 24ቱ የስማርት የኮሙኒኬሽን ክፍሎች ከነገ በስቲያ በተመሳሳይ ሰዓት ተመርቀው በይፋ ስራ እንደሚጀምሩም ገልጸዋል።

በሁሉም ክልሎች፣በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በተመረጡ አስር የፌዴራል ተቋማት የተገነቡት እነዚህ ስማርት የኮሙኒኬሽን ክፍሎች ግንባታ አንድ ዓመት መውሰዱንም ነው የገለጹት።

ቀጣይነት ያለው አገልግሎት እንዲሰጡም ለባለሙያዎች የአጠቃቀም ማንዋልና የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎቹን በሁሉም ተቋማት ለማዳረስ ከክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ጋር እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026