
አዲስ አበባ፤ግንቦት 18/2017(ኢዜአ)፦የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የቆዳ ፋብሪካዎችን ምርትና ምርታማነት ማሳደግ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማረም ላይ መስራት እንዳለበት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ።
ቋሚ ኮሚው የአምራች ኢንዱስትሪ ኢንስቲትዩት የቆዳና ቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪ ምርምር ልማት ማዕከል የ2014/2015 በጀት አመት የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ላይ ውይይት አካሂዷል።
በዚህ ወቅት የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሰረት ዳምጤ እንደገለጹት ተቋሙ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የክዋኔ ኦዲት ግኝት ቀርቦበት እንደነበረ አስታውሰዋል።
ከቀረቡበት የኦዲት ግኝቶች ውስጥ ክፍተቶችን ለማሻሻል የሄደበት ርቀት ጥሩ ቢሆንም ቀሪ እርምጃዎችን የሚጠይቁ ተግባራት መኖራቸውን አንስተዋል።
በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን ክፍተት ከመቅረፍ አንጻር በቀጣይ መስራት እንደሚገባው አመልክተዋል።
የቆዳ ፋብሪካዎች ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የምርት ስብጥርን የሚጨምሩ ተግባራት ላይ ክፍተቶች መኖራቸውን አንስተው፤ በዚህ ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።
የምርምር ስራን በማጠናከር ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በዘርፉ ከመፍጠር አንጻር ከአጋር አካላት ጋር መስራትን እንደሚገባውም የኦዲት ግኝቱ እንደሚያሳይ አስታውቀዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በዚህ ወቅት የቆዳና ሌጦ ዘርፍ ትልቅ ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች መካከል መሆኑን አንስተዋል።
ይህንንም ተከትሎ በዘርፉ ስርነቀል ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ስራዎች ባለፉት አመታት መከናወናቸውን አስታውቀዋል።
የኦዲት ግኝቱን በመውሰድ በትኩረት መሰራቱን አንስተው በቀጣይ ባልተስተካከሉት ላይ እርምት ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።
የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተሩ ሚልኬሳ ጀገማ በበኩላቸው ተቋሙ የተሰጠውን የኦዲት ግኝት ተከትሎ በርካታ የማስተካከያ ተግባራትን ማከናወኑን ተናግረዋል።
በቀጣይም ቀሪ ክፍተቶችን የማስተካከያ ስራዎች እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አራሬ ሞሲሳ በሰጡት ማጠቃለያ ዘርፉን ውጤታማ ከማድረግ አኳያ ሰፊ ስራ መስራት እንደሚገባ አንስተዋል።
ተቋሙ የድርጊት መርሃ ግብር እስከ ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓም ድረስ መላክ እንዳሚገባው እና በየሶስት ወር የደረሰበትን ማሳወቅ እንዳለበትም አሳስበዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026