አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2017(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ ሜሎኒ ጋር የሁለቱን ሃገራት የኢንቨስትመንት ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
መሪዎቹ በመተግበር ላይ ያለውን የትብብር አፈፃፀም በመገምገም በባለብዙ ወገን እንዲሁም አዳዲስ የትብብር መስኮችን በተሻሻለ የኢንቨስትመንት መጠን ለመከወን የሚቻልባቸው ጉዳይች ላይ ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ ኃላፊነት ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ የጣሊያን መሪዎች ጋር የሁለትዮሽ ትብብሮችን ለማጠናከር ሰርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጥቅምት 2015 ጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒ ወደ ኃላፊነት በመጡ በአጭር ጊዜ በሮም በመገኘት በምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የሰላም እና ፀጥታ እንዲሁም በልማት ረገድ ጣልያን ለኢትዮጵያ ልማት የምታደርገውን ድጋፍ አስመልክቶ ውይይት ተደርጎ ነበር።
ከዚህ ውይይት በኋላም መሪዎቹ ጠንካራ የስራ ግንኙነት የመሠረቱ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ በ2016 ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል።
ቀጣይ ውይይቶችም በጣሊያን እንዲሁም ሌላ ሀገራት ላይ በተካሄዱ ባለብዙ ወገን መድረኮች ተካሂደዋል።
ጣሊያን የኢትዮጵያ ልማት ቁልፍ አጋር ስትሆን በኢንደስትሪ ብሎም እንደ ጤና፣ ግብርና እና ባሕላዊ ቅርስ ጥበቃ የረጅም ዘመን ደጋፊም መሆኗም ተገልጿል።
የጣሊያን ኩባንያዎች እና የጣሊያን የልማት ትብብር ተቋም ሥራዎችን በንቃት እየደገፉ እንደሚገኙም ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሁለቱ መሪዎች በመጨረሻ ስብሰባቸው ለዘላቂ ልማት እና የተሻሻለ ኢንቨስትመንት ያላቸውን የጋራ ርዕይ አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025