የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ ሜሎኒ ጋር ተወያዩ

May 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2017(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ ሜሎኒ ጋር የሁለቱን ሃገራት የኢንቨስትመንት ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

መሪዎቹ በመተግበር ላይ ያለውን የትብብር አፈፃፀም በመገምገም በባለብዙ ወገን እንዲሁም አዳዲስ የትብብር መስኮችን በተሻሻለ የኢንቨስትመንት መጠን ለመከወን የሚቻልባቸው ጉዳይች ላይ ተወያይተዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ ኃላፊነት ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ የጣሊያን መሪዎች ጋር የሁለትዮሽ ትብብሮችን ለማጠናከር ሰርተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጥቅምት 2015 ጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒ ወደ ኃላፊነት በመጡ በአጭር ጊዜ በሮም በመገኘት በምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የሰላም እና ፀጥታ እንዲሁም በልማት ረገድ ጣልያን ለኢትዮጵያ ልማት የምታደርገውን ድጋፍ አስመልክቶ ውይይት ተደርጎ ነበር።

ከዚህ ውይይት በኋላም መሪዎቹ ጠንካራ የስራ ግንኙነት የመሠረቱ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ በ2016 ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል።

ቀጣይ ውይይቶችም በጣሊያን እንዲሁም ሌላ ሀገራት ላይ በተካሄዱ ባለብዙ ወገን መድረኮች ተካሂደዋል።

ጣሊያን የኢትዮጵያ ልማት ቁልፍ አጋር ስትሆን በኢንደስትሪ ብሎም እንደ ጤና፣ ግብርና እና ባሕላዊ ቅርስ ጥበቃ የረጅም ዘመን ደጋፊም መሆኗም ተገልጿል።

የጣሊያን ኩባንያዎች እና የጣሊያን የልማት ትብብር ተቋም ሥራዎችን በንቃት እየደገፉ እንደሚገኙም ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ሁለቱ መሪዎች በመጨረሻ ስብሰባቸው ለዘላቂ ልማት እና የተሻሻለ ኢንቨስትመንት ያላቸውን የጋራ ርዕይ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025