
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2017(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ ሜሎኒ ጋር የሁለቱን ሃገራት የኢንቨስትመንት ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
መሪዎቹ በመተግበር ላይ ያለውን የትብብር አፈፃፀም በመገምገም በባለብዙ ወገን እንዲሁም አዳዲስ የትብብር መስኮችን በተሻሻለ የኢንቨስትመንት መጠን ለመከወን የሚቻልባቸው ጉዳይች ላይ ተወያይተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ ኃላፊነት ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ የጣሊያን መሪዎች ጋር የሁለትዮሽ ትብብሮችን ለማጠናከር ሰርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጥቅምት 2015 ጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒ ወደ ኃላፊነት በመጡ በአጭር ጊዜ በሮም በመገኘት በምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የሰላም እና ፀጥታ እንዲሁም በልማት ረገድ ጣልያን ለኢትዮጵያ ልማት የምታደርገውን ድጋፍ አስመልክቶ ውይይት ተደርጎ ነበር።
ከዚህ ውይይት በኋላም መሪዎቹ ጠንካራ የስራ ግንኙነት የመሠረቱ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ በ2016 ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል።
ቀጣይ ውይይቶችም በጣሊያን እንዲሁም ሌላ ሀገራት ላይ በተካሄዱ ባለብዙ ወገን መድረኮች ተካሂደዋል።
ጣሊያን የኢትዮጵያ ልማት ቁልፍ አጋር ስትሆን በኢንደስትሪ ብሎም እንደ ጤና፣ ግብርና እና ባሕላዊ ቅርስ ጥበቃ የረጅም ዘመን ደጋፊም መሆኗም ተገልጿል።
የጣሊያን ኩባንያዎች እና የጣሊያን የልማት ትብብር ተቋም ሥራዎችን በንቃት እየደገፉ እንደሚገኙም ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሁለቱ መሪዎች በመጨረሻ ስብሰባቸው ለዘላቂ ልማት እና የተሻሻለ ኢንቨስትመንት ያላቸውን የጋራ ርዕይ አረጋግጠዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025