
አሶሳ፤ ግንቦት 20/2017(ኢዜአ):- የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ዘርፉን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ሚኒስትሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስራ የጀመሩትን 24 ስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎች በአሶሳ ከተማ ተገኝተው ዛሬ አስጀምረዋል።

ያስጀመሩትም የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በ10 የፌዴራል ተቋማት፣ በሁሉም ክልሎች እና ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች መሆኑም ተገልጿል።
የኢኖቪሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ መንግስት የቴክኖሎጂ ዘርፉን በማዘመን ዜጎች የተቀላጠፈ እና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው ።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በቀላሉ እንዲገናኙና ስራቸውን እንዲያሳልጡ የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ይህም ወጪ እና ጊዜን የሚቆጥብ እንዲሁም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልምድን የሚያዳብር ነው ብለዋል።
የስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎቹ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን የያዙ የድምጽ እና የቪዲዮ ፕላትፎርም ያላቸው መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ስራ መጀመር ኢትዮጵያ ለያዘቸው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ አንዱ ማሳያ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በቀጣይም ዘርፉ በሀገር ሁለንተናዊ ጥቅም የሚኖረውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎችን በጥንቃቄ መጠቀም እና ከወቅቱ ጋር በሚዛመዱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ማዘመን እንደሚገባ አሳስበዋል።
በማስጀመሪያ መረሃ ግብር ላይ የሚኒስቴሩ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026