
አሶሳ፤ ግንቦት 20/2017(ኢዜአ):- የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ዘርፉን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ሚኒስትሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስራ የጀመሩትን 24 ስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎች በአሶሳ ከተማ ተገኝተው ዛሬ አስጀምረዋል።

ያስጀመሩትም የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በ10 የፌዴራል ተቋማት፣ በሁሉም ክልሎች እና ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች መሆኑም ተገልጿል።
የኢኖቪሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ መንግስት የቴክኖሎጂ ዘርፉን በማዘመን ዜጎች የተቀላጠፈ እና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው ።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በቀላሉ እንዲገናኙና ስራቸውን እንዲያሳልጡ የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ይህም ወጪ እና ጊዜን የሚቆጥብ እንዲሁም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልምድን የሚያዳብር ነው ብለዋል።
የስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎቹ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን የያዙ የድምጽ እና የቪዲዮ ፕላትፎርም ያላቸው መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ስራ መጀመር ኢትዮጵያ ለያዘቸው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ አንዱ ማሳያ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በቀጣይም ዘርፉ በሀገር ሁለንተናዊ ጥቅም የሚኖረውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎችን በጥንቃቄ መጠቀም እና ከወቅቱ ጋር በሚዛመዱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ማዘመን እንደሚገባ አሳስበዋል።
በማስጀመሪያ መረሃ ግብር ላይ የሚኒስቴሩ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025