አሶሳ፤ ግንቦት 20/2017(ኢዜአ):- የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ዘርፉን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ሚኒስትሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስራ የጀመሩትን 24 ስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎች በአሶሳ ከተማ ተገኝተው ዛሬ አስጀምረዋል።
ያስጀመሩትም የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በ10 የፌዴራል ተቋማት፣ በሁሉም ክልሎች እና ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች መሆኑም ተገልጿል።
የኢኖቪሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ መንግስት የቴክኖሎጂ ዘርፉን በማዘመን ዜጎች የተቀላጠፈ እና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው ።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በቀላሉ እንዲገናኙና ስራቸውን እንዲያሳልጡ የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ይህም ወጪ እና ጊዜን የሚቆጥብ እንዲሁም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልምድን የሚያዳብር ነው ብለዋል።
የስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎቹ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን የያዙ የድምጽ እና የቪዲዮ ፕላትፎርም ያላቸው መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ስራ መጀመር ኢትዮጵያ ለያዘቸው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ አንዱ ማሳያ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በቀጣይም ዘርፉ በሀገር ሁለንተናዊ ጥቅም የሚኖረውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎችን በጥንቃቄ መጠቀም እና ከወቅቱ ጋር በሚዛመዱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ማዘመን እንደሚገባ አሳስበዋል።
በማስጀመሪያ መረሃ ግብር ላይ የሚኒስቴሩ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025