የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ዘርፉን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል- ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

May 30, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ግንቦት 20/2017(ኢዜአ):- የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ዘርፉን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተናገሩ።

ሚኒስትሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስራ የጀመሩትን 24 ስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎች በአሶሳ ከተማ ተገኝተው ዛሬ አስጀምረዋል።


ያስጀመሩትም የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በ10 የፌዴራል ተቋማት፣ በሁሉም ክልሎች እና ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች መሆኑም ተገልጿል።

የኢኖቪሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ መንግስት የቴክኖሎጂ ዘርፉን በማዘመን ዜጎች የተቀላጠፈ እና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው ።

የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በቀላሉ እንዲገናኙና ስራቸውን እንዲያሳልጡ የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህም ወጪ እና ጊዜን የሚቆጥብ እንዲሁም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልምድን የሚያዳብር ነው ብለዋል።

የስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎቹ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን የያዙ የድምጽ እና የቪዲዮ ፕላትፎርም ያላቸው መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ስራ መጀመር ኢትዮጵያ ለያዘቸው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ አንዱ ማሳያ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በቀጣይም ዘርፉ በሀገር ሁለንተናዊ ጥቅም የሚኖረውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎችን በጥንቃቄ መጠቀም እና ከወቅቱ ጋር በሚዛመዱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ማዘመን እንደሚገባ አሳስበዋል።

በማስጀመሪያ መረሃ ግብር ላይ የሚኒስቴሩ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026