አዲስ አበባ፤ግንቦት 20/2017(ኢዜአ)፡-ስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች ቀልጣፋ እና ውጤታማ የስራ ተግባቦት እንዲፈጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ገለጹ።
በ10 የፌደራል ተቋማት፣በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የተገነቡ ስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች ተመርቀው በይፋ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎቹ የተለያዩ ቦታዎች ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትን በቀላሉ እንዲገናኙና ስራቸውን እንዲያሳልጡ የሚያስችሉ ናቸው።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ይህንን ስኬት እንዲመዘገብ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎቹ ለመረጃ ልውውጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተናግረዋል።
ማዕከላቱ ውጤታማ የስራ ግንኙነት እንዲፈጠር በማድረግ አስፈላጊ የሆነ ፈጣን ተግባቦት እንዲፈጠር የሚያግዙ መሆኑን ገልጸዋል።
ለአመራር ሰጭ አካላትም ፈጣን የሆነ ውሳኔ ለመስጠትም ያስችላሉ ነው ያሉት።
በቀጣይም እነዚህን ማዕከላት በሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስማርት የኮሙኒኬሽን ስርዓትን ለማጠናከር አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ስራ አስፈጻሚ ጌታቸው መለሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ማዕከላቱ ውጤታማ የዲጅታል ኮሙኒኬሽን ስርዓትን መፍጠራቸውን አንስተዋል።
እንዲሁም ሀገራዊ የዲጂታላይዜሽን ስራን ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025