
አዲስ አበባ፤ግንቦት 20/2017(ኢዜአ)፡-ስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች ቀልጣፋ እና ውጤታማ የስራ ተግባቦት እንዲፈጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ገለጹ።
በ10 የፌደራል ተቋማት፣በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የተገነቡ ስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች ተመርቀው በይፋ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎቹ የተለያዩ ቦታዎች ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትን በቀላሉ እንዲገናኙና ስራቸውን እንዲያሳልጡ የሚያስችሉ ናቸው።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ይህንን ስኬት እንዲመዘገብ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎቹ ለመረጃ ልውውጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተናግረዋል።
ማዕከላቱ ውጤታማ የስራ ግንኙነት እንዲፈጠር በማድረግ አስፈላጊ የሆነ ፈጣን ተግባቦት እንዲፈጠር የሚያግዙ መሆኑን ገልጸዋል።
ለአመራር ሰጭ አካላትም ፈጣን የሆነ ውሳኔ ለመስጠትም ያስችላሉ ነው ያሉት።
በቀጣይም እነዚህን ማዕከላት በሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስማርት የኮሙኒኬሽን ስርዓትን ለማጠናከር አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ስራ አስፈጻሚ ጌታቸው መለሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ማዕከላቱ ውጤታማ የዲጅታል ኮሙኒኬሽን ስርዓትን መፍጠራቸውን አንስተዋል።
እንዲሁም ሀገራዊ የዲጂታላይዜሽን ስራን ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026