ሠመራ፤ግንቦት 20/2017(ኢዜአ)፡- ስራ የጀመሩት የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎች የዲጂታል የአገልግሎት ስርዓት ለማቀላጠፍ የሚያስችሉ መሆናቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።
በዛሬው ዕለት ሚኒስቴሩ በአፋር ክልል ሠመራ ከተማ የተገነባውን የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍልን ስራ አስጀምሯል።
በዕለቱ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽሩን አለማየሁ(ዶ/ር) እንደገለጹት፥ለአገልግሎት የበቁት የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች የዲጂታል አገልግሎት ስርዓቶችን በመጠቀም የተቀላጠፈ ስራን ማከናወን ይቻላል።
ስራዎችን በቅንጅት በማከናወን በአንድ ማዕከል አገልግሎት በማግኘት የህብረተሰብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።
በዚህም ጊዜንና ገንዘብን በመቆጠብ ረገድ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ያመለከቱት ሚኒስትር ዴኤታው፥የቴክኖሎጂውን አገልግሎት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአፋር ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ኮሚሽነር ኢንጂነር መሀመድ ሰኢድ በበኩላቸው፥የስማርት ኮሙኒኬሸን ማሳለጫው ጥራት ያለውና አስተማማኝ አገልግሎት የሚሰጥ የቴክኖሎጂ ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢንጂነር መሀመድ፥የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ቴክኖሎጂውን በማመቻቸቱ ምስጋና አቅርበዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በ10 የፌዴራል ተቋማት፣ በሁሉም ክልሎች እና ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ዛሬ ስራ መጀመራቸው ቀደም ሲል መገለጹ ይታወሳል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025