
ሠመራ፤ግንቦት 20/2017(ኢዜአ)፡- ስራ የጀመሩት የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎች የዲጂታል የአገልግሎት ስርዓት ለማቀላጠፍ የሚያስችሉ መሆናቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።
በዛሬው ዕለት ሚኒስቴሩ በአፋር ክልል ሠመራ ከተማ የተገነባውን የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍልን ስራ አስጀምሯል።
በዕለቱ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽሩን አለማየሁ(ዶ/ር) እንደገለጹት፥ለአገልግሎት የበቁት የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች የዲጂታል አገልግሎት ስርዓቶችን በመጠቀም የተቀላጠፈ ስራን ማከናወን ይቻላል።
ስራዎችን በቅንጅት በማከናወን በአንድ ማዕከል አገልግሎት በማግኘት የህብረተሰብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።
በዚህም ጊዜንና ገንዘብን በመቆጠብ ረገድ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ያመለከቱት ሚኒስትር ዴኤታው፥የቴክኖሎጂውን አገልግሎት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአፋር ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ኮሚሽነር ኢንጂነር መሀመድ ሰኢድ በበኩላቸው፥የስማርት ኮሙኒኬሸን ማሳለጫው ጥራት ያለውና አስተማማኝ አገልግሎት የሚሰጥ የቴክኖሎጂ ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢንጂነር መሀመድ፥የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ቴክኖሎጂውን በማመቻቸቱ ምስጋና አቅርበዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በ10 የፌዴራል ተቋማት፣ በሁሉም ክልሎች እና ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ዛሬ ስራ መጀመራቸው ቀደም ሲል መገለጹ ይታወሳል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026