
ሠመራ፤ግንቦት 20/2017(ኢዜአ)፡- ስራ የጀመሩት የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳላጫ ክፍሎች የዲጂታል የአገልግሎት ስርዓት ለማቀላጠፍ የሚያስችሉ መሆናቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።
በዛሬው ዕለት ሚኒስቴሩ በአፋር ክልል ሠመራ ከተማ የተገነባውን የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍልን ስራ አስጀምሯል።
በዕለቱ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽሩን አለማየሁ(ዶ/ር) እንደገለጹት፥ለአገልግሎት የበቁት የስማርት ኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍሎች የዲጂታል አገልግሎት ስርዓቶችን በመጠቀም የተቀላጠፈ ስራን ማከናወን ይቻላል።
ስራዎችን በቅንጅት በማከናወን በአንድ ማዕከል አገልግሎት በማግኘት የህብረተሰብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።
በዚህም ጊዜንና ገንዘብን በመቆጠብ ረገድ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ያመለከቱት ሚኒስትር ዴኤታው፥የቴክኖሎጂውን አገልግሎት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአፋር ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ኮሚሽነር ኢንጂነር መሀመድ ሰኢድ በበኩላቸው፥የስማርት ኮሙኒኬሸን ማሳለጫው ጥራት ያለውና አስተማማኝ አገልግሎት የሚሰጥ የቴክኖሎጂ ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢንጂነር መሀመድ፥የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ቴክኖሎጂውን በማመቻቸቱ ምስጋና አቅርበዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች በ10 የፌዴራል ተቋማት፣ በሁሉም ክልሎች እና ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ዛሬ ስራ መጀመራቸው ቀደም ሲል መገለጹ ይታወሳል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026