
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2017(ኢዜአ)፦የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና መዲናዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የላቀ ሚና እንዳለው የአዲስ አበባ ከተማ ኢኖቬሽና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
አዲስ አበባን ስማርት ሲቲ ለማድረግ ከተያዙት እቅዶች መካከል በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ ፈጣን አገልግሎቶችን መተግበር አንዱና ዋነኛው ሲሆን የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ደግሞ ለስኬቱ ከፍተኛ አበርክቶ አለው።
ይህን ተከትሎ ቢሮው የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠናን አስመልክቶ በየካ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ ወጣቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ- ግብር አካሒዷል።

የቢሮው የጽሕፈት ቤት ኃላፊ ግሩም አብተው በመርሃ-ግብሩ መክፈቻ ላይ እንዳሉት፤ የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በዲጂታል ቴከኖሎጂ ብቃት ያለው ዜጋ ለማፍራት ከፍተኛ ሚና አለው ።
የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ከተማዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ የተያዙትን እቅዶች ለማሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ ቴክኖሎጂ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቴዎድሮስ ማስረሻ በበኩላቸው፤ የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠናው ቴክኖሎጂን የተረዳና በብቃት የሚጠቀም ወጣት ለመፍጠር ማስቻሉን ነው የጠቀሱት።
በዚሀም በክፍለ ከተማው 25 ሺህ የሚጠጉ ወጣቶችና የመንግስት ሰራተኞች ስልጠናውን በተመለከተ ግንዛቤ እንዲወስዱ መደረጉን ገልጸዋል።
ወጣቶቹ ስልጠናውን ከመከታተል ባለፈ በተጨባጭ ስራ ፈጣሪና ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን መገንዘብ መቻሉንም ጠቅሰዋል።

ወጣት ይገረም አበራ በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ድረ-ገጾችን በማበልፀግ፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በዳታ ሳይንስና በአንድሮይድ ዘርፎች ክህሎቱን ማዳበሩን ተናግሯል።
ወጣት ማርታ መከተ በበኩሏ ስልጠናው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፎች አዳዲስ እና ዘመናዊ የሆኑ እውቀቶችን የሚያስይዝ መሆኑን ተከትሎ የራሴ የሆኑ ስራዎችን ለመፍጠር አስችሎኛል ብላለች።
ስልጠናው በዋናነት በዘርፉ ስራ ለመፍጠር ከፍተኛ እድል ይዞ መምጣቱንም ወጣቶቹ አስታውቀዋል ።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026